Sunday 30 November 2014

ምርጫ መሳተፍ በመርዕ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ወይስ ኢህአዴግን ማጀብ? – ከግርማ ሰይፉ ማሩ

November 30,2014

ሰዎች በማንኛውም መንገድ ሸብረክ ሸብረክ የሚሉ ከሆነ መርህ አልባ መሆናቸውን ከማሳየት ውጭ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ ባለፈው ሳምነት ፍኖተ ነፃነት ላይ ወጣቱ ፀሃፊ ኢዮኤል ፍስሃ ዳምጤ ለምን እንደምንፈራ ቁልጭ አድርጎ አሳይቶን ነበር፡፡ የገዢዎቻችን በትር የበረታብን በእነርሱ ጥንካሬ ሳይሆን ከፍርሃት በመጣ ዝምታችን እንደሆነ አስምሮበታል፡፡ መፍትሔውም ከፍርሃት መላቀቅና ዝምታውን ማፍረስ ነው፡፡ በዛሬው ፅሁፌ ማንሳት የፈለኩት ደግሞ ለምን ሸብረክ ሸብረክ እንደምንል ነው፡፡
ለምንድነው ኮሽ ሲል ደንግጠን ከቆምንበት “መርዕ” ከምንለው አስተሳሰብ የምንሸራተት? እንዲህ ከሆነ ቀድሞውንም መርዕ አልነበረንም ማለት ነው፡፡ መርዕ ብለን የምንይዘው አሰተሳሰብ በእኔ እምነት ለምናደርገው እንቅስቃሴ የማዕዘን ድንጋይ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ መርዕ ሸርተት ስንል ቀጥሎ የምናገኝው ሌላ የተሻለ ማዕዘን የሚሆን ድንጋይ ሳይሆን ድጥ ወይመ ማጥ ነው የሚሆነው፡፡ ብዙዎች መርዕ የሚመስላቸው በአቋራጭ የሚፈልጉትን ግብ የሚያሳካ አጭር መንገድ አድርገው ይወስዱታል፡፡ ይህ አቋራጭ መንገድ ግን ብዙን ጊዜ ወደ ሌላ ውጥንቅጥ ከመውሰድ አልፎ ለስኬት ሲያበቃ አይታይም፡፡
Girma Siefu

ግልፅ ያልሆነ የህይወት ግብ ያለን ሰዎች የምንሄድበትን ስለማናውቅ ሌሎች በሄዱበት ተከትለን እንነጉዳለን፣ ሌሎች ግባቸውን ሲያሳኩ እኛ የበይ ተመልካች መሆናችን አይቀርም፡፡ ግባችን ግልፅ ያለመሆኑ መድረሻችንን ብቻ ሳይሆን መነሻችንንም ስሚያዛባው ከየት ተነስተን የት እንደምንደርስ፣ እንዴት እንደምንደርስ እንዳናውቅ ያደርገናል፡፡ መርዕ ማለት አሁን ካለንብት ቦታ ተነስተን ወደምንፈልገው ቦታ ለመድረስ የምንጓዝበት ፍኖተ ካርታ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በአሰተሳሰብ ብቻ ሳይሆን በተግባርም ልክ መሆን ያለበት ነው፡፡ አንድ አንድ ሰዎች የምንፈልገውን ግብ ለማሳካት ማነኛውንም መንገድ መጠቀም ችግር የለውም ይላሉ፡፡ ይህ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው /the end justify the means/ የሚባለው ዓይነት መሆኑ ሲሆን፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ ሌሎች የምንሄድበት መንገድ እንደ ወጤቱ ሁሉ መርዕ ላይ መመስረት አለበት የሚሉ ናቸው /The means is equally important as the end/:: በግሌ የማምነውም የምከተለውም የኋለኛውን አማራጭ ነው፡፡ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው የስግብግቦች መንገድ ነው ብዬ በፅኑ ስለማምን፡፡
ሰሞነኛ ወደ ሆነው የምርጫ አጀንዳ እና በመርዕ ላይ የተመሰረተው የአንድነት ፓርቲ ምርጫ እሳተፋለሁ ውሳኔ እንዴት መታየት እንዳለበት በአጭሩ ይህን አቋም ለደገፉም ሆነ ለተቃወሙ ማሰረዳት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ አንድነት ፓርቲ ስልጣን የሚገኘው በህዝብ ድምፅ ነው የሚል መርዕ አለው፡፡ የህዝብ ድምፅ የሚገኘው ደግሞ በምርጫ ወቅት መራጩ ህዝብ በሚሰጠው ካርድ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ በምርጫ የህዝብ ድምፅ ይገኛል ማለት ነው፡፡ ብዙዎች ምርጫ ለመሳተፍ እኩል ሜዳ ያሰፈልጋል ይላሉ፡፡ ትክክል ነው እኔም አምንበታለሁ፡፡ ሜዳውን ትክክል ከሚያደርገው አንዱ ጉዳይ የምርጫ ቦርድ ገለልተኝነት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የምርጫ ቦርድ ገለልተኛ ካልሆነ ማለትም ሜዳው ትክክል ካልሆነ ስልጣን በሌላም መንገድ መያዝ ተቀባይነት አለው የሚል መከራከሪያ ለማቅረብም ሰበብ ይሆናል፡፡
ስልጣን በተለያየ መንገድ ለመያዝ እንደሚቻል አማራጭ ማሳየት አንድ ጉዳይ ሆኖ እኛ የመረጥነው ብቻ ልክ ነው ማለትም ተገቢ አይደለም፡፡ በተገኘው መንገድ ለመያዝ መሞከር ግን መርዕ አልባ ያደርገናል፡፡ ሰላማዊ ትግል እከተላለሁ ብሎ በሰላማዊ ትግል መርዕዎች አምናለሁ የሚል ማታ-ማታ ወይም ቅዳሜና-እሁድ በሌላ መንገድ ልሞክር የሚል ከሆነ መርዕ አልባነት ነው፡፡ በእኔ እምነት ችግር ያለው የምርጫ ሜዳ ላይ ከሆነ የምርጫው ሜዳው ለማስተካከል ምን አድርገናል? ከሚለው መነሳት አለበት፡፡ ስልጣን የመያዣው መንግድ ኮሮኮንች በዝቶበታል ማለት ኮሮኮንቹን እንዴት እናሻሽል ወደሚል ሊገፋን ይገባል፡፡
ሁሉም ሰው መረዳት ያለበት ገዢው ፓርቲ የምርጫ ሜዳውን ያጠበበው ወይም ኮሮኮንች እንዲበዛበት ያደረገው አውቆ ነው፡፡ ሜዳው ደግሞ የጠበበን ደግሞ አማራጭ አለን የምንል ፓርቲዎች ነን፡፡ አማርጭ ለማቅረብ እድል ስንነፈግ መጠየቅ ያለብን አንድ መስረታዊ ጥያቄ አማራጭ የተከለከለው ህዝብ ምንም ማድረግ አለበት የሚለው ነው? አማራጭ የሚፈልግ ህዝብ ድንጋይ ወይም ጠብመንጃ ይዞ አማራጭ አትከልክሉን ቢል ነው የሚሻለው ወይስ የምርጫ ካርድ ይዞ? አንድነት የመረጠው መስመር የምርጫ ካርድ ይዞ ቢሆን ይሻላል የሚለውን ነው፡፡ ይህ በምንም ዓይነት ሌሎች የመረጡት መስመር አይሰራም ማለት አይደለም፡፡ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭውን እንደ መርዕ የተቀበለ ብዙ ሌላ አማራጭ ሊያስብ፣ ሊተገብር ይችላል፡፡ ችግሩ የእኛ ካልሆነ ብሎ የሌሎችን ምርጫ ለማክበር አለመፈለጉ ላይ ነው፡፡
ETHIOPIA ELECTIONS
በሀገራችን ኢትዮጵያ በ1997 ከተደረገው ምርጫ ውጭ ህዝቡ በምርጫ እንዲሳተፍ የምርጫ ካርድ እንዲወስድ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በተገቢው መልኩና ደረጃ ተቀስቅሶዋል የሚል እምነት የለኝ፡፡ ከ1997 በፊት ምርጫ መወዳድር ወያኔን ማጀብ ነው እያልን ምርጫ የሚወዳደሩትን ብቻ ሳይሆን መራጩንም ተሰፋ እያስቆረጥን ኖረናል፡፡ ይህን ምርጫ የማጣጣል ስትራቴጂያችንን በደንብ የተረዳው ገዢው ፓርቲ የራሱን መራጮችና ተመራጮች እያዘጋጀ ውድድር ሲያድርግ ነበር፡፡ እንደዚያም ሆኖ ህዝቡ በምርጫ ካርዱ ቅሬታውን ሲገልፅ እንደ ነበር የገዢው ፓርቲ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴእታ የነበሩት አቶ ኤርሚያስ ለገሠ “የመለስ ትሩፋቶች” በሚለው መፅሃፍ አስነብቦናል፡፡ ስለዚህ የአንድነት ቤተሰቦች ምርጫ እንሳተፋለን ስንል መራጮቻችን እንዲመዘገቡ እናደርጋለን ማለት ነው፡፡ የእኛ መራጮች ሲመዘገቡ፣ ገዢው ፓርቲ የእኔ ብሎ ያስመዘገባቸውም ቢሆኑ እኛን ለመምረጥ እንዲችሉ መሸሸጊያ እንሰጣቸዋለን፡፡
ብዙ ሰው መረዳት ያለበት የምርጫ ቅስቀሳ የሚጀመርበት ወቅት መራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሳምንት ሲቀረው ነው (በ1997 ቀድሞ የምርጫ ቅስቀሳ ተጀምሮ ነበር)፡፡ ለዚህ ነው ገዢው ፓርቲ ሁል ጊዜ የሚጮሁት ካርድ ያልያዙ ናቸው የሚለው፡፡ ያስመዘገባቸውን ስለሚያውቅ ነው፡፡ የእኛ መራጮች ካርድ ባልያዙበት ሁኔታ የፈለገ አማላይ የሆነ ለሀገር የሚጠቅም አማራጭ ብናቀርብ ለማሸነፍ ያለን እድል አነስተኛ ነው፡፡
ማስተላለፍ የፈለኩት ነጥብ ምርጫ እገባለሁ-አልገባም በሚል ዥዋዝዌ ስንጫወት ደጋፊዎቻችን በመራጭነት ሳይመዘገቡ እንዳይቀሩ በአንድነት በኩል የተወሰደው እርምጃ ትልቅ ፖለቲካ ውሳኔ ነው፡፡ የምርጫ ፓርቲ መሆናችን የሚታወቅ ቢሆንም እስከ አሁን በተቃዋሚ ፓርቲዎች መስመር ምርጫ መግባትና አለመግባት በቁርጥ ቀድሞ ስለማይወሰን መራጮች ሁለት ልብ እየሆኑ ከጫወታ ውጭ ሲደረጉ ከርመዋል፡፡ ይህ እንዳይደግም መራጮች እንዲመዘገቡ እና በምርጫው ሙሉ ሂደት በንቃት እንዲሳተፉ ይህን አቋም መያዝ እጅግ አስፈላጊ እና ጠቃሚ ነበር፡፡ ሁሉም እንደሚረዳው ያልተመዘገበ ደግሞ አይመርጥም፣ ያልመረጠ ደግሞ ድምፁ እንዲከበር ዘብ ሊቆም አይችለም፡፡ ድምፃችን ይከበር የሚለው እንቅስቃሴ የሚጀምረው ከህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እሰከ ድምፅ ቆጠራ ድረስ ይዘልቃል፡፡
ጎበዝ ሰላማዊና ህጋዊ ትግል እናደርጋልን ስንል የሰላማዊና ህጋዊ ትግል መርዖዎችን ጠንቅቀን መረዳት የግድ ይለናል፡፡ በስላማዊ ትግል ዋናው ግብ የህዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ ሲሆን፣ ስልጣን መያዝ የሚፈልግ ፓርቲ የህዝብ ይሁንታ ማግኘት የግድ ይለዋል፡፡ ይህ ደግሞ በምርጫ የሚገኝ ነው፡፡ ምርጫውን የህዝብ ፖለቲካ ተሳትፎ መለኪያ አድርገን ለመውስድ ቁርጠኞች መሆን የግድ ይለናል፡፡
ቸር ይግጠመን

ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ!


ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።
ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይ የብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።
የማንዋሉን ዓላማዎች በሚገልፀው ክፍል ደግም “… የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት የልማት ሰራዊት ግንባታን ወይም የፓለቲካ ሰራዊት ግንባታ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደራጀና በተናቀጀ ሁኔታ በማቀጣጠልና በማስቀጠል … ምርጫ 2007 ውጤታማ ለማድረግ እና የኢህአዴግን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ነው” በማለት ተቋማቱን የኢህአዴግ የምርጫ መሣሪያ መሆናቸውን፤ ግባቸውም የኢህአዴግ አሸናፊነትን ማረጋገጥ መሆኑ ይገልፃል።
በገጽ 3 ላይ ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች “በኢህአዴግ ላይ ያላቸው አቋም የወረደ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በማንኛውም ተቃውሞ ድምፅ ከተጠሩ፤ ሰልፍ የሚያደምቁ፤ ተቃውሞን ከግብ ለማድረስ ሁነኛ መሳሪያ ናቸው። ተማሪዎች በየትኛውም ሐገር እንደታየው አደባባይን የመያዝ ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ የማሳደም እድላቸው የሰፋ በመሆኑ ከዚህም ሲያልፍ፤ የኢህአዴግ ምከታን በመቃወም ለጠላት ጎራ ተሰልፈው የመታጠቅ እድላቸው ከፍተኛ ነው” ሲል “በወጣቱ እጠላለሁ” የሚለው የህወሓት/ኢህአዴግን ስጋት አፍረጥርጦ ያወጣል። ትንሽ ወረድ ብሎ ደግሞ “በተለይ በአሁኑ ሰዓት ፈተና ላይ የጣለን የምርጫ ጉዳይ እንደምናሸንፍ ቃል የተያዘለት ቢሆንም፤ ፈተናዎች የሚፈጠሩት በህዝብ እና በራሱ ታማኝ ባልሆኑ ሃይሎች ማለትም በመንግስት ክንፍ አይቀለበስም ብሎ ማሰብ አይቻልም። በዚህም ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት እና ለሁከት እና ለብጥብጥ መሳሪያ ሊሆን የሚችለው የህዝብ ክንፍ የተማረው ሃይል ሊሆን ስለሚችል ሊታሰብበት ይገባል” ሲል በተማረው ወጣትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠራተኞች ላይ ያለው ጥርጣሬና ፍርሃት ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃል።

የ2007 ምርጫ በህወሓት ሹማምንት ላይ የፈጠረውን ጭንቀት በዚህ ሰነድ ላይ በገሀድ የሚታይ በመሆኑ እያንዳንዱ ዓረፍተ ነገር በጥንቃቄ ሊነበብና ሊተነተን የሚገባው ነው። ለምሳሌ በገጽ 6 ላይ ስለዩኒቨርስቲ ተማሪ ሲገልጽ “የአመፅ እና የብጥብጥ መነሻ ሊሆን የሚችል ሀይል መሆኑን በአክራሪዎች ሲጠለፍ፤ ከመንግስት ሃይማኖቱን እየመረጠ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ፤ በጅማ ዩኒቨርስቲ፤ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ እና በሌሎችም ትምህርቱን ትቶ ሲኮበልል ተመልክተናል” ይላል። ለተማሪዎች፣ ከመንግሥት እና ከሃይማኖት አንዱን እንዲመርጡ ተደርጎ ሃይማኖታቸውን የመረጡ መኖራቸውን እና ይህ ደግሞ አደገኛ ነገር መሆኑን ነው ይህ ዓረፍተ ነገር የሚነግረን። ለመሆኑ ይህ ምን የሚሉት ምርጫ ነው? በእንዴት ያለ ሥርዓት ነው ዜጎች ከመንግስትና ከሃይማኖት አንዱን ምረጡ የሚባለው? እንዲህ ዓይነት ምርጫ ቀርቦ ሃይማኖትን መምረጥ እንዲህ ክፉ ነገር የሆነው ለምንድነው? ይህ ጉዳይ ብቻውን ብዙ የሚያነጋገር ነገር አለው።
በገጽ 8 ላይ ደግሞ “ከፍተኛ አመራሩ ተቋማዊ ለውጥ እንዲሁም የትምህርት ልማት ሰራዊት ግንባታ ቴክኒካዊ ሳይሆን ፓለቲካዊ ጉዳይ መሆኑን ተገንዝቦ ካለእርሱ ባለቤትነትና ቀጥተኛ ተሳትፎ ሰራዊት መገንባት እንደማይቻል በመገንዘብ የመሪነት ሚናውን ካለምንም ማወላዳት መወጣት ይጠበቅበታል” በማለት እየተሠራ ያለው የፓርቲ ወገንተኛ የሆነ ፓለቲካ መሆኑን ብቻ ሳይሆን የትምህርት ተቋማት መሪዎች ዋና ተልዕኮ ትምህርት ማስተማር ሳይሆን የወያኔ ፖለቲካን ማስፈጸም መሆኑን ምንም ሳይጎረብጠው ፍርጥርጡን ያወጣዋል። ትንሽ ወረድ ብሎም “የጋራ መግባባት የምንለካው በመጀመሪያ ለምርጫው የኢህአዴግ የድጋፍ የድል ሰራዊት ብዛት ነው” በማለት ከላይ ያለውን በማጠናከር ወገንተኛነቱም ለኢህአዴግ መሆኑ ያውጃል። በመጨረሻም “ … ሁሉም የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው ለምርጫው በሚያዘጋጁት የድጋፍ ሃይል ይወሰናል” በማለት የአካዳሚ ነፃነት ብቻ ሳይሆን የከፍተኛ ትምህርት ሥርዓትን ለቀብር ያዘጋጃል።
ይህ ነው የህወሓት የትምህርት ፓሊሲ! የዩኒቨስቲዎች ቁጥር ለማመን በሚቸግር መጠን ቢጨምር፤ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ቅበላ በብዙ መቶኛዎች ቢያድግ ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው። በእንዲህ ዓይነቱ ፓሊሲ ከተገነባ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም ይገኛል የምንለው ፋይዳ ምንድነው?
ህወሓት በገሀድ በጠላትነት የፈረጃቸው የአገራችን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ መምህራንና ሠራተኞች ይህንን አሳሳቢ ጉዳይ በአጽንኦት እንዲመለከቱ ግንቦት 7፣ የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ያሳስባል። ትውልድንም የትምህርት ሥርዓቱንም የማዳን ግንባር ቀደም ኃላፊነት በተማሪዎችና በመምህራን የወደቀ ሸክም ነው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል። መላው የትምህርት ሥርዓት ለአንድ ፓርቲ የምርጫ ውድድር መሣሪያነት ሲውል ማየት እና የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች የሥራ አፈፃፀም የሚወሰነው ለገዢው ፓርቲ ባስገኙት ድምጽ ብዛት ነው መባሉ፤ እነሱም ይኸንን ተቀብለው መሥራት መቀጠላቸውን የመሰለ አሳፋሪ ነገር በአካዳሚያ ውስጥ የለም። የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞቻችን ይህን ውርደት መቀበል የለባቸውም። ሰነዱ ህወሓት ከፍተኛ ትምህርትን የሚመለከትበት ዕይታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነውና ለምርጫ ወቅት ብቻ የተዘጋጀ የአጭር ጊዜ መመሪያ ተደርጎ መወሰድ የለበትም። ይህ ሰነድ ህወሓት፣ ተማሪዎችንና መምህራንን እንደጠላት፤ ተቋማቱን ደግሞ ጠላትን እንደመቆጣጠሪያ መሣሪያ እንደሚመለከት፤ ይህ ዕይታው ደግሞ ቋሚ መሆኑ በግልጽ ያሳያል። በህወሓት ዕይታ ከተገነቡ ተቋማት ምን ዓይነት ትምህርት ይገኛል?
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ኃላፊዎችና ፕሬዚዳንቶች ሆይ! ለገዛ ራሳችሁ ክብር፣ ለአካዳሚ ነፃነት፣ ለትውልድ ስትሉ በዚህ መመሪያ ላይ አምጹ! “እንቢ፣ አሻፈረን፣ በዚህ መመሪያ አንገዛም” በሉ! የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎናችሁ ይቆማል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት)

‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ


በላይ ማናዬ

ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡

ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡

ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስር ቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…እያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ‹ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ቦታው ላይ ስንደርስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሶስት ፖሊሶች ተከብቦ ቀድመውን ከደረሱ ወዳጆቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡ ከአጥር ወዲህ እና ወዲያ ማዶ ሆነን ግማሽ አካል ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ ደስ አለን፤ ተመስገንም ደስታው በመላ ፊቱ ሲበራ ተመለከትን፡፡ በደስታው ድጋሜ ደስ ተሰኘን፡፡ በእኛ በኩል ትንሽ ስለ ጤንነቱ፣ በእሱ በኩል ስለቤተሰብ እና ስለእኛ ደህንነት ተጠያየቅን፡፡ በመካከላችን ትንሽ ዝምታ ሰፈነ፡፡ እኛም ተመስገንም ቀና ብለን ፖሊሶችን ተመለከትን፡፡ ከዚያም ተመስገን ጥያቄ ወረወረ፡፡

‹‹ውጭ ያለው እንዴት ነው? አንድነትና ሰማያዊ….›› ተሜ የጀመረውን ሳይጨርስ ሁለቱ ፖሊሶች አንባረቁብን፡፡
‹‹ፖለቲካ አታውራ! እናንተ ፖለቲካ አታውሩ! ዝም ብላችሁ ሌላ ሌላ አውሩ!...›› አሉን ፖሊሶች አንዴ እኛን አንዴ ከአጥር ማዶ የተቀመጠውን ተመስጋንን እየተመለከቱ፡፡ የፖለቲካ ድርጅቶችን ስም መጥራት ፖለቲካ ማውራት ሆኖ ተሰማቸው፣ እዚያ ለነበሩ ፖሊሶች፡፡ የአንድነትን እና የሰማያዊን ስም ጠርቶ ተሜ ምን ሊያወራ እንደፈለገ እንኳ ለመስማት አልተዘጋጁም፡፡ በየዕለቱ መረጃ የሚያነፈንፍ፣ ያገኘውን መረጃ ደግሞ ወደህዝብ የሚያደርስ ሙያ ላይ እንደነበር ለእነሱ አልገባቸውም፡፡ አዎ መረጃ ምን ያህል እንደሚርብ ለፖሊሶቹ የተገለጸላቸው አልመሰለኝም፤ ለዚያውም ለጋዜጠኛ፡፡

ተሜ ጋር ልናወራ ያሰብነው ብዙ አብይ ጉዳዮች ቢኖሩም ክልከላው የሚያወላዳ አልሆነም፡፡ በበኩሌ በኋላ ተመስገን ላይ ሊያደርሱበት የሚችሉት ጫና ይኖራል ከሚል ርዕሱን መቀየሩን መርጬ ነበር፡፡ ተመስገን ግን ‹‹እናውራበት›› በሚል ትንሽ ከፖሊሶቹ ጋር ተከራከረ፡፡ ተሜ ድፍረቱ በብዕሩ ብቻ አይደለም፡፡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ የማይል ብርቱ ሰው መሆኑን ከሁኔታው አነበብኩ፡፡

በመሐል ላይ ሌሎች እስረኞችን እንዲጠሩልን ስም ዝርዝር ሰጥተን ስለነበር ሲዘገዩ ጊዜ ‹‹እነ ክንፈሚካኤልና አሳምነውን ጥሩልን እንጂ!›› አልናቸው፡፡ አንደኛው ፖሊስ ቆጣ ብሎ ‹‹ቆይ እሱ ጋር ጨርሱ!›› አለን፡፡ ከተመስገን ጋር ያለንን ቆይታ ማለቱ ነበር፡፡ እኛም እስኪመጡ እንደምንጨርስ በመጥቀስ አስጠሩልን አልናቸው፡፡ በዚህ መሐል ትንሽ ጭቅጭቅ ድጋሜ ተፈጠረ፡፡ ‹‹እንዲያውም ስማቸውን በትክክል አልጻፋችሁም፤ ስለዚህ አንጠራላችሁም አሉን፡፡›› እኛም የሰጠናቸውን የስም ዝርዝር የጻፉት የራሳቸው ባልደረቦች እንጂ እኛ አለመሆናችንን ጠቅሰን ነገርናቸው፡፡

ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚመስል መልኩ አንጠራላችሁም አሉን፡፡ ‹‹በቃ አምጣው እንደገና አስተካክለው እንዲጽፉ አድርገን እናምጣው!›› አልናቸው፡፡ በእርግጥ ትክክለኛ ምክንያታቸው የስም ስህተት እንዳልሆነ እናውቅ ነበር፡፡ ሲጀመር አሳምነው ፅጌን ከእኛ ከወጣቶች ይልቅ እነሱ ከበረሃ ጀምረው ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ ስለሆነም ‹‹እገሌ የሚባል ሰው የለም፤ እዚሁ ተወለደ ካላላችሁን›› እያሉ ሲናገሩ በውስጤ እየሳቅሁ ነበር፡፡ እንዲያውም፣ ‹‹አዲስ ታሰረ ካላላችሁ በቀር አዲስ እንደማይወለድ ታውቃላችሁ፤ ሴትና ወንድ የት ይገናኛሉና ነው!›› አልኩ፡፡ የግዳቸውን ፈገግ አሉ፡፡

በዚህ መሰል ጭቅጭቅ ከተመስገን ጋር ያለንን ጊዜ ተሻሙብን፡፡ ይህ የገባው ተመስገን ደሳለኝ በጭቅጭቁ ጣልቃ ገብቶ፣ ‹‹ሰዎቹ ከአዲስ አበባ ነው የመጡት፡፡ ስለሆነም ከሩቅ ቦታ መጥተው ሳያገኟቸው ቢመለሱ ደስ አይልም›› አላቸው፡፡ ወዲያው አንደኛው ወደ እኛ ዞሮ ‹‹ናትናኤል መኮንንን የት ነው የምታውቀው?›› አለኝ፡፡ ጥያቄውን ወደጓደኛየም ወሰደው፡፡ ‹‹ይህን ጥያቄ ምን አመጣው›› ብዬ ጥያቄውን በጥያቄ ከመመለሴ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ቀበል አድርጎ ‹‹ኢትዮጵያዊ ወገኑን ሳያውቀውም ቢሆን መጠየቅ ይችላል!›› አለ፡፡ ተመስገን ተቆርቋሪነቱ ደስ ይላል፡፡ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እስረኞቹ ሊጠሩልን ስምምነት ላይ ደረስን፡፡ እስኪመጡ ድረስም ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ‹‹ከፖለቲካ ውጭ›› ባለ ድባብ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡

ተሜ ስለሚዲያ አብዝቶ ጠየቀኝ፡፡ ያለው ሁኔታ ከሚያውቀው እውነታ እንዳልተለወጠ ገለጽኩለት፡፡ ከዚያም ወደወንድሙ ዞሮ ስለቤተሰባዊ ጉዳዮች ሲያወራ ዓይኖቼን ወዳስጠራናቸው እስረኞች መምጫ አማትር ያዝኩ፡፡ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ከርቀት አንድ ላይ ሆነው ሲመጡ ተመለከትኩ፡፡ ከፖሊሶች ጋር ባለው እሰጣ ገባ ስሜቴ ተረብሾ ነበር፡፡ ይህ ስሜቴ ግን ድንገት ሶስቱ ሰዎች ከርቀት በፈገግታ ታጅበው ወደ እኛ ሲመጡ ሳይ በንኖ ጠፋ፡፡

ሞገደኛው አበበ ቀስቶ እና የተጓደለው ጤናው ጉዳይ

ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ካለንበት ስፍራ ደርሰው ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አቤት እንዴት ደስ እንዳላቸው! ሙሉ ፊታቸው ያበራል፡፡ ‹‹እኛን ልትጠይቁ መጣችሁ?›› እያሉ በደስታ ተቁነጠነጡ፡፡ እውነት ለመናገር ደስታው የእነሱ ሳይሆን የእኛ ነበር፡፡ በበኩሌ በእስር ላይ ያሉ ወንድም እህቶቼን መጠየቅ ምን አይነት የህሊና እረፍትና ደስታ እንደሚሰጠኝ የማውቀው እኔው ነኝ፡፡

ይህ ደስታችን ታዲያ ተመስገን ደሳለኝ ጋር በነበረው መልኩ ድንገት ደፈረሰ፡፡ ፖሊሶቹ አሁንም እሳት ለበሱ፡፡ ከውጭ ያለውን ነገር የተራቡት እነ ክንፈሚካኤል እነዚያን የፓርቲ ስሞች ጠቅሰው ጥያቄ ሰነዘሩ፡፡ ‹‹አንድነትና ሰማያዊ…›› ካፋቸው ቀልበው ፖሊሶቹ አንባረቁ፡፡ ‹‹አንተ ፖለቲካ አታውራ!›› በማለት ያዙኝ ልቀቁኝ አሉ፡፡ እንዲያውም ምንም ሳናወራ ተነሱና ግቡ አሏቸው፡፡ በዚህ ጊዜ አበበ ቀስቶ በኃይለ ቃል መልሶ ፖሊሶቹ ላይ አፈጠጠ፡፡ ፖሊሶቹ ትንሽ ድንግጥ በማለት ‹‹ሌላ ሌላ አውሩ በቃ!›› አሉን፡፡

ዝዋይ እስር ቤት ካሉ እስረኞች ጋር የሚገናኝ ጠያቂ ‹‹ደህና ነህ፣ እንዴት ነህ…›› ብቻ ብሎ እንዲመለስ ነው የሚፈለገው፡፡ ከሁሉም ጋር ያለውን ማህበራዊና የጤና ሁኔታ አንስተን ስንጨዋወት አበበ ቀስቶ ወደእኔ አንገቱን ሰገግ አድርጎ ‹‹አሞኛል፣ በብርቱ ከታመምኩ ቆይቻለሁ›› አለኝ፡፡ ከዚህ ቀደም በጤናው ላይ እከል እንደገጠመው አውቅ ነበር፡፡ የአሁኑ ህመሙ ምን ይሆን በሚል የበለጠ እንዲነግረኝ እኔም አንገቴን ሰገግ አድርጌ ጆሮዎቼን ሰጠሁት፡፡

‹‹የሚያመኝ ይሄን የጆሮየን አካባቢ ነው፡፡ በብርቱ ታምሜያለሁ፡፡ አብሮኝ የሚተኛው ናትናኤል መኮንን ባይሆን ኑሮ ምን እንደሚውጠኝ አላውቅም፡፡ ቁስል አበጅቶ መጥፎ ጠረንም ፈጥሯል›› አለኝ፡፡ እኔም የህመሙ ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቅኩት፡፡

‹‹ያኔ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እያለሁ የደረሰብኝ ድብደባ ነው ዛሬም የሚያሰቃየኝ›› አለኝና ከዚያ ወዲህ እንዴት እየተሰቃየ እንዳለ አስከትሎ አስረዳኝ፡፡ እኔም ‹‹ህክምና…›› ሳልጨርሰው ተቀበለኝ፡፡ ‹‹ህክምና የሚባለውን ተወው፡፡ ይሄው ስንት ጊዜ እንዲያሳክሙኝ የምጮኸው! ሰበቡ አያልቅባቸውም! ምንም በቂ ህክምና አላገኘሁም፡፡ መቼስ….›› ብሎ ያ ከደቂቃዎች በፊት በሳቅ፣ ከዚያም በንዴት ውስጥ የነበረው ቆፍጣናውና ቀጭኑ ፖለቲከኛ በትካዜ አንገቱን ደፋ፡፡ ውስጤ በማላውቀው ስሜት ተላወሰ፡፡ አበበ ቀስቶ በስካርቭ ጨርቅ ሙሉ ጆሮ ግንዱን ጠምጥሞ የመጣበት ምክንያት ገባኝ፡፡ ቁስሉን ለመሸፈን ነው፡፡

ከአበበ ጋር ይህን ስናወራ ሌሎች ወዳጆቼ ከእነ አሳምነው እና ናትናኤል ጋር ስለተለያዩ ጉዳዮች (‹ከፖለቲካ ውጭ›) እያወሩ ነበር፡፡ ‹‹እስኪ ደግሞ ከእነሱ ጋር አውራ፣ ጊዜህን እኔ ብቻ ወሰድኩብህ›› አለኝ አበበ ቀስቶ ወደ ናትናኤልና አሳምነው እየተመለከተ፡፡ እኔም በአለችው ትንሽ ደቂቃ ከሌሎቹ ጋር ጨዋታ ያዝኩ፡፡ በዚህ መሐል ግን ቀልቤ የአበበ ቀስቶ ጤንነት ላይ ነበር፡፡ እንዴት ሰው አካሉ እንዲያ ቆስሎ ህክምና አይሰጠውም?

ስንብት

በፖሊሶች ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ለሰላሳ ደቂቃዎች ብቻ የነበረን ቆይታ ማብቃቱን ስንረዳ 30 ደቂቃ ምን ያህል አጭር እንደሆነ ተገነዘብን፡፡ ስድስት ሰዓት ደርሶም ስለነበር መለያየታችን ግድ ሆነ፡፡ ስንገናኝ እንዳደረግነው ሁሉ እንደገና ለስንብትም ተቃቀፍን፡፡ በእቅፎቻችን መካከል የተሰነቀረው አጥር ደግሞ የመለያየታችን ደንቃራነት ማሳያ ነበር፡፡

ከእነ አበበ ቀስቶ ጋር ያለኝን ስንብት ጨርሼ ወደ ተመስገን ደሳለኝ ስጠጋ በእጆቹ አንገቴን ሳብ አድርጎ ወደ ጆሮዬ ጠጋ በማለት ‹‹ስርዓት ሲፈርስ የሚያደርገውን ያጣል፡፡ ስርዓቱ እየፈረሰ ነው›› አለኝ፡፡ ምንም አልመለስኩለትም፡፡ በእጆቼ ትከሻውን መታ መታ በማድረግ የተናገረውን መስማቴን አረጋገጥኩለት፡፡

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ


‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡


በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡

ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡

አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡

ቂሊንጦ ከእነ በፍቃዱ ጋር ስንጨዋወት ስለእስክንድር ነጋ ትሁትነት፣ አስተዋይነት፣ ሰላማዊነት እያነሱ ሰላምታ እንዳደርስላቸው ጠየቁኝ፡፡ እኔም እስክንድር ነጋን ሳውቀው በትሁትነቱ፣ በአስተዋይነቱና በሰላማዊነቱ ነው፡፡ ዛሬ በነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተበሳጭቶ ነበር የተመለከትኩት፡፡ ያ ፈገግታው ከፊቱ ብን ብሎ ጠፍቶ ‹‹ያገባኛል!›› ሲልበት የነበረውን ስሜት ግር አለኝ፡፡ ካልነኩት የማይነካ ሰው ሲነኩት ትንታግ ነው፡፡ እስክንድር እዛ ስሜት ውስጥ የገባው ተገድዶ ነበር፡፡ ሊጠይቁት የመጡትን ሰዎች አብዛኞቹን አላስገባም ማለታቸው ሳያንስ ከገቡትም መካከል የምታወራውን እኔ ልምረጥልህ በሚል ግብዝነት አባርረዋል፡፡ እስክንድር ይህን አይቶ ዝም ማለት አልቻለም፡፡ ስለሆነም እንዲህ አለ፤

‹‹…እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው! ስለሀገሬ ያገባኛል!››

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በአዲስ አበባ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ዋሉ

ዘጠኙ የተቃዋሚ ትብብር ፓርቲዎች የጠሩትን "የ24 ሰዓት የአደባባይ ተቃውሞ" (ከህዳር 27, 2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28) አስመልክቶ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በአዲስ አበባ ጎዳናዎች እየተዘዋወሩ ቅስቀሳ ማድረጋቸውን ከሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች አንዷ የሆነችው እየሩሳሌም ተስፋው ውሏቸውን እንዲህ በማለት በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች፣
ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን ሙሉውን ዘገባ ያንብቡት
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በአዲስ አበባ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ዋሉ
ዘጠኙ የተቃዋሚ ትብብር ፓርቲዎች የጠሩትን
ECADFORUM.COM

Saturday 29 November 2014

Teen’s gang rape in Addis Ababa sounds alarm

November 29, 2014

More than 70 percent of Ethiopian women face physical and sexual violence

by Tigist Geme
Hanna Lalango, 16, died on Nov. 1, from a brutal gang rape after five men kidnapped and held her captive for several days in Ethiopia’s capital, Addis Ababa. Hanna attended a private high school in the city’s Ayer Tena neighborhood.More than 70 percent of Ethiopian women face physical and sexual violence
On Oct. 1, the day of her kidnapping, Hanna, the youngest of six siblings, “complained about not feeling well” before she left for school. “She was a typical young girl … a timid and respectful child,” Hanna’s brother told Blen Sahilu, who first posted the story on Facebook, as part of the online#JusticeForHanna campaign. “She was really nice.”
Hanna reportedly left school around 4 p.m. local time and got on a taxi that already had a couple of passengers. It is unclear at what point Hanna knew she was being kidnapped. But the culprits allegedly threatened the teen with knife and took her to one of the suspect’s house. Reports vary but Hanna’s father told the local media she was raped for at least five days.
Hanna’s kidnappers had other plans. They apparently contacted her sisters by phone, perhaps to kidnap them as well. They met the sisters at an arranged place, driving the same minibus, and reportedly asked them to come along. When they refused, the men drove off, exclaiming, “You won’t see your sister then!” A few days later, the suspects left Hanna to die in an abandoned area in the outskirts of the city. Hanna was found unconscious on Oct. 11 and taken to hospital.
“My phone rang 11 days after Hanna disappeared, it was the voice I missed,” Hanna’s father told the U.S.-based Admas Radio last week. “She was weak and exhausted.” For the next few days the family spent going between various referral hospitals and waiting to be admitted. Among other injuries, Hanna suffered from fistula and lost her battle 19 days after she was found. She reportedly identified three of the five suspects from her hospital bed.
On Nov. 19, police brought five suspects before the First Appearance Court in Addis Ababa, according to local reports. During a hearing attended by journalists and women right’s groups, one of the suspects pleaded innocence and all five denied the allegations, telling the court their initial confessions were obtained under duress. The police denied torturing the suspects and asked for 14 days to conduct further investigation.
Hanna could have been saved. The police were slow to investigate the case as a sexual crime. The hospitals failed to treat Hanna’s case with the outmost urgency the situation demanded. I broke down in tears as I read about Hanna’s ordeal. I tried to imagine what she might have felt as her captors took turns to satisfy their desires. I imagined how helpless she might have felt. I imagined Hanna worrying and speculating about how to deal with this tragedy or even tell her parents. Hanna spent days on the streets after suffering a brutal gang rape. It took her few days to call her parents and seek help. It remains unclear whether this was planned or a random incident. But Hanna’s story is far from isolated.

Guilt and sexual trauma

Ethiopia is a deeply patriarchal, closed and conservative country. It has one of the highest rates of sexual violence in the world. More than 70 percent of Ethiopian women face physical and sexual violence, according to a study by the World Health Organization (WHO). Seven percent of girls surveyed by WHO reported experiencing sexual abuse before the age of 15. Seventeen percent said their first sexual experience was forced. The country also has one of the highest rates of bridal kidnapping or marriage by abduction.
Most women and girls keep incidents of rape and sexual abuse secret to avoid societal shunning. About 39 percent never talk to anyone about the violence and the violations they endure, according to WHO. Even fewer women ask authorities for help. Some 53 percent feared repercussions and threats from their partners, while another 37 percent “considered the violence ‘normal’ or ‘not serious,’” the WHO report said.
Worse still, most gender-based violence is solved through family arbitration and socially sanctioned compensation for the victim’s family. As a result, women often don’t feel the need to go public with their story. Therefore, it is not surprising that Hanna’s kidnappers reportedly sent “elders” seeking reconciliation with her parents even as Hanna clung to her last breath in a hospital bed.
Hanna’s story took me back to Addis Ababa, where people walk past you even when they can clearly see that you are in danger. It is a city where the police yell at the victim for running away from a man forcing her into an unwanted relationship or sexual intimacy.
“Addis Ababa is a jungle, be careful,” a friend advised me when I first moved to the city. It didn’t take me long to understand what she meant. In the 10 years that I lived in the city, I learned to cope with endless gazes and widely accepted catcalling. Addis Ababa is one of the country’s few major metropolises. To be sure, city women fare relatively better than their rural counterparts: They drive new cars, they are fashionistas, they hang out at upscale cafes along the famed Bole road, they watch American movies at the city’s upscale Enda Mall and Movie Theater (enjoying popcorn), and they go to sauna and spa every weekend.
But this city of beautiful women has another less known, darker face. In fact, the city’s cosmopolitan character gives the impression that Addis women don’t deal with sexual violence. Hanna’s heart-wrenching story also reminded me of an incident that I will never forget.
I was a young lecturer at Addis Ababa University, then in my early 20s. One afternoon, a colleague from the university invited me for lunch. He took me to a place he said was his favorite near Arat Kilo neighborhood. The restaurant was located a walking distance of off the main road and looked like a place no self-respecting man would take a girl on the first date — a hole-in-the-wall in a residential neighborhood on a barely paved road. After we ate lunch, my colleague went to the bar and whispered something to one of the servers, and returned to ask me to go to the backside for “more privacy.” By then I was growing suspicious of his mannerisms and refused the request. First he tried to persuade me and then he reached and pulled my arms to force me to go with him.
The restaurant owner and customers stood puzzled as I struggled to get away from him. To cover up his brazen acts, he started pretending as if we were married or in some kind of relationship. One of the guys at the restaurant offered to help. I asked him to find a police at which point the restaurant’s owner insisted that I leave. “I don’t want police to come here and ask me to be a witness,” he said. I told him I wouldn’t leave until I know that I am safe.
Shortly afterwards, the gentleman returned with two young policemen. For a minute I felt safe. I told the cops what happened. “It is all your fault,” one of the officers exclaimed. “Why would you go for lunch with him unless you are interested.” I felt insulted and humiliated in front of the restaurant’s patrons. I made it home safe that day but said nothing of my colleague who continued to threaten to get me fired for years unless I slept with him.
As a counselor at AAU, my students came to me with their problems thinking I was better of. I was older than most, but my lot was not better. I received no protection from the university or law enforcement. My students told of sleepless nights worrying about how they would make it to class the next day amid men who wake up early in the morning to do nothing but harass and intimidate them.
In contrast with those in rural areas, a woman in Addis maybe educated and assertive but they are not protected. Their daily ordeal consists of finding another route to school to escape from the guy who threatened to kill them or maim their face. It means making up stories to tell your parents about the bruises on your nose after a boyfriend punched you, or a redeye or a bruise on your chin from a guy you refused to date. It is an untold story of countless women who live with the trauma and guilt of sexual violence. There is simply no good reason or justification for a man to put his hand on a woman. And no women should go through this in the 21st century. But there are few guarantees.

A wakeup call

Hanna’s story received scant attention from the government-run media. Hanna’s story saw the light of day thanks to social media. So far only a handful of Ethiopian outlets carried the story, offering a brief account of Hanna’s kidnapping and rape. Last week, the Ministry of Women’s Affairs held a press conference and pledged to assist with the investigation. However, the Ministry is a political instrument for the country’s rulers and lacks the power and necessary resources to address the pervasive violence against women in Ethiopia. The officials spend more time ballyhooing the government’s record on gender equality to donors while ignoring the normalized sexual and physical violence against women. Independent human rights work is severely restricted. There are no community-based initiatives that can deal with the culturally sanctioned harassment, abuse and discrimination against women.
Hanna’s horrific death should serve as a wakeup call for all Ethiopian women. Sexual and physical violence does not discriminate. Educated or not, teenage or fully-grown women — every woman in Ethiopia is a potential victim. As Sahilu rightly noted, “rape is not about sex,” it is about traditional notions of power. Our society shames and disempowers victims while the rapists are let off the hook under the cover of culture and traditionalism. Nothing could ever bring back Hanna but her death is an opportune moment for Ethiopian women to unite and fight to end gender-based violence. It is the least we can do to honor Hanna.
Tigist Geme is a former lecturer at Addis Ababa University. She currently lives in Washington, D.C.
Source: ALJAZEERA

Wednesday 26 November 2014

SA Has Most Prisoners In Africa and the Second is Ethiopia.

According to the report, South Africa has recorded a total of 165 395 inmates in April 2014. This was followed by Ethiopia with 93 044 and Morocco with 72 816 prisoners.
The study revealed 2.3% of South Africa’s inmates in April were female, while 0.3% of the prisoners were minors.
There were 27.8% pre-trial detainees and 5.3% foreigners.
South Africa’s official capacity is 119 890 inmates, which means occupancy level is 127.7% over.
The report further found western African countries locked up 46 people per 100 000 population. In southern African countries this figure spiked to 205 people per 100 000 population.
Other significant findings were that almost half of the world’s prisoners are in the United States, China or Russia – countries which barely account for a quarter of the world’s population.
There are more than 10.2 million prisoners around the world.
“It is of grave concern that there are now over 10.2 million men, women and children held in penal institutions throughout the world. What is of graver concern is that the world prison population continues to rise, despite the fact that imprisonment is a highly expensive option for governments, as well as being inappropriate and ineffective for the majority of prisoners who come from minority and marginalised groups, or who are mentally ill or who are alcohol and drug abusers,” said the director of the ICPS, Peter Bennett.
“The International Centre for Prison Studies calls on those governments with high or rising rates of imprisonment to reduce their prison populations and to seek alternatives to custody in the interests of good economy, effectiveness in sentencing and the achievement of internationally agreed standards.”

Tuesday 25 November 2014

የኢህአዴግን የአባልነት ፎርም አንሞላም ያሉ ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

በአዊ ዞን  የኢህአዴግን የአባልነት ፎርም አንሞላም ያሉ ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

ኀዳር ፲፮(አስራ ስድስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :- በአዊ ዞን አንከሻ ወረዳ ውስጥ የሚማሩ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች የኢህአዴግን የአባልነት መሙያ ፎርም ወስደው እንዲመዘገቡ በርእሰ መምህራቸው አማካኝነት ቢጠየቁም፣ ከ700 ያላነሱ ተማሪዎች ድርጊቱን ተቃውመዋል።

ተማሪዎቹ የአባልነት ቅጹን በሁለት ቀናት ውስጥ የማይሞሉ ከሆነ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ለፈተናም እንደማይቀርቡ ተነግሯቸዋል። “ከእንግዲህ ኢህአዴግ የሚባል ነገር ማየት አንፈልግም” ያሉት ተማሪዎች ፣ በትምህርት ቤት አስተዳደሪዎች የቀረበላቸውን ውትወታ ውድቅ አድርገዋል።
ምንም እንኳ አንዳንድ ተማሪዎች በስጋት የአባልነት ፎርም ቢሞሉም አብዛኛው ተማሪ ግን ጥሎ መውጣቱን ከአካባቢው ያገኘነው መረጃ አመልክቷል። ጉዳዩን በማስመልከት ጥያቄ ያቀረብንላቸው የመኢአድ ምክት ሃለፊ አቶ ዘሪሁን ባንቲ፣ ተማሪዎች በሁለት ቀናት ውስጥ ፎርም የማይሞሉ ከሆነ ከትምህርት ገበታቸው እንደሚባረሩ ገልጸው፣ መንግስት በአቋሙ ከጸና በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሊያቋርጡ ይችላሉ ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በአካባቢው በተቃዋሚዎች ላይ እየደረሰ ያለው መዋከብ መጨመሩን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፣ የእርሳቸው ልጅ የተቃዋሚ አባል ልጅ ናት በሚል ሰኞ እለት ከትምህርት ቤት ስትመለስ በአንድ የካደሬ ልጅ ተደብድባ ወደ ህክምና መወሰዱዋን ገልጸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሰካም።
ኢህአዴግ የሁለተኛ እና ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስገድዶ አባል ለማድረግ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ በተጨማሪ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎችም የአባልነት ፎርም እንደሚሉ እንቅስቃሴ ጀምሯል። እድሜያቸው ከ12 አመት በታች የሆኑ ተማሪዎች ” ታዳጊ የኢህአዴግ አባል” ተብለው ይመዘገባሉ። ኢህአዴግ በመላ አገሪቱ 6 ሚሊዮን አባላት እንዳሉት ይገልጻል። ይሁን እንጅ አብዛኞቹ ድርጅቱን ለጥቅምና ለህልውና ብለው የሚቀላቀሉ በመሆኑ፣ ለኢህአዴግ ህልውና ስጋት መፍጠራቸውን አቶ አዲሱ ለገሰ ለድርጅቱ አመራሮች በጻፉት ወረቀት ላይ ገልጸዋል። ኢህአዴግ ነባር አባላቱን በሁለተኛ ደረጃና በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለመተካት ቢያስብም አብዛኛው ተማሪ ኢህአዴግን መጥላቱ እቅዱ ሊሳካ እንደማይችል የድርጅቱ አባላት ይናገራሉ። የትምህርት ሚኒስቴር ሰሞኑን ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባዘጋጀው የትምህርት ሰራዊት ግንባታ ወረቅት ላይ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በኢህአዴግ ላይ ጥላቻ እንዳላቸው ማተቱን መዘገባችን ይታወሳል።

Monday 24 November 2014

በሰሜን የአገሪቱ ክፍል ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየታከሄደ ነው

ኀዳር ፲፭(አስራ አምስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ መንግስት ከማሃል አገር ሰፍረው የቆዩትን የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ሁመራና ሌሎች የድንበር አካባቢዎች በስፋት እያሰማራ መሆኑን ወታደራዊ ምንጮች ገለጹ።

ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ከኤርትራ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየታየ መሆኑን የገለጹት ምንጮች፣ ምክንያቱ ደግሞ ኢህአዴግን በሃይል አስገድደው ለማውረድ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች ጥቃት ሊሰነዝሩ ይችላሉ የሚለው ስጋት እያየለ በመምጣቱ ሳይሆን እንደማይቀር ይገምታሉ። በአካባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆ መሄድ ገዢውን ፓርቲ እንዳሳሰበው የሚናገሩት ምንጮች፣ በተለይም በጠረፍ አካባቢ የሚኖረው ወጣት የተቃዋሚ ሃይሎችን ድንበር እያቋረጠ በስፋት እየተቀላቀለ መሆኑ፣ ሃይሉን እንዲያጠናክርና በድንበሩ አካባቢ ከፍተኛ ቁጥጥር ለማድረግ ሳያሰነሳሳው እንዳልቀረ ይናገራሉ።
መንግስት የተወሰነ ጦሩን ወደ ሱዳን በማስገባት የተቃዋሚ ሃይሎችን እንቅስቃሴ ለመግታት ከሱዳን ጋር ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።

ሱዳን 2 ሺ ኢትዮጵያውያንን በጉበትና በኤድስ ተጠቅተዋል በሚል ልታባርር ነው

ኀዳር ፲፭(አስራ አምስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-በሱዳን የሰሜን ግዛት በምትገኘዋ ኤል ዳባ የሚኖሩ ከ2 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ተጠርንፈው ወደ ካርቱም የተላኩ ሲሆን፣ የከተማዋ ባላስልጣናት ኢትዮጵያውያኑ ሄፒታይተስ ሲ የተባለው የጉበት በሽታና የኤድስ ቫይረስ ስላለባቸው መላካቸውን ገልጸዋል።


የኤል ዳባ ፖሊስ ኮሚሽነር  ኢስላም አብደል ራህማን ለሱዳን ትሪቢዩን እንደተናገሩት የግዛቱ ባለስልጣናት በውጭ አገር ዜጎች  ላይ በድንገት ባደረጉት የህክምና ምርምራ ከ15 ኢትዮጵያውያን መካከል 6ቱ ሄፒታይተስ ሲ የሚባለው የጉበት በሽታ እንደተገኘባቸው፣ እንዲሁም በድጋሜ ከተመረመሩ 54 ኢትዮጵያውያን መካከል በ5 ቱ ላይ በሽታው መገኘቱን ተናግረዋል። በምርምራው ሁለት ኢትዮጵያኖች በኤች አይ ቪ ቫይረስ መያዛቸው በዘገባው ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ ፖሊስ በግዛቱ የሚኖሩ 2 ሺ ኢትዮጵያውያንን በአንድ ላይ በመጠረዝ ካርቱም ለሚገኘው ለፓስፖርትና ኢምግሬሽን መስሪያ ቤት አስረክበዋል። በአሁኑ ሰአት በግዛቱ ውስጥ 10 የውጭ አገር ዜጎች ብቻ እንደሚገኙ ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።
ድርጊቱ ፍጹም ዘረኝነት የተሞላበትና ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በላይ የተዋረዱ ዜጎች መሆናቸውን እንደሚያሳይ ሱዳን የሚገኙ ስደተኞች ገልጸዋል። በሌሎች አገር ዜጎች ላይ የማይፈጸም ድርጊት በኢትዮጵያውያን ላይ ይፈጸማል የሚሉት ነዋሪዎች፣ ኤች አይ ቪ ኤድስም ሆነ የጉበት በሽታ በየትኛውም አገር ተሰዶ መኖርን እንደማይከለክል ይገልጻሉ። በሽታው ሰበብ መሆኑን የሚገለጹት ስደተኞች፣ የኢትዮጵያ መንግስት ሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከታዋሚዎች ጋር ያብራሉ በሚል ስጋት ከሱዳን መንግስት ጋር ያቀነባበረው ድርጊት መሆኑን ይገልጻሉ።
ሱዳን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያውያንን በሰበብ አስባቡ ከአገሯ እያስወጣች ነው።

Saturday 22 November 2014

አንድነት ፓርቲ በምርጫ እንደሚሳተፍ አስታወቀ

ኀዳር ፲፪(አስራ ሁለትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-አንድነት ለዴሞክራሲያዊና ለፍትሕ ፓርቲ በመጪው 5ኛ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡

ፓርቲው በኢትዮጵያ ውስጥ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ለማድረግ ሁኔታዎች ምቹ አለመሆናቸውን ቢጠቅስም “ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሆኖ ህዝቡ እንዲሳተፍ በመቀስቀስና በማበረታታት የተዘጋውን የዴሞክራሲ በር በምርጫ ካርዱ ሊያስከፍት እንደሚችል ከፍተኛ እምነት” እንዳለው አስታውቋል።
መንግስት  የመድበለ ፓርቲን ስርዓት ለማጎልበት ምንም ዓይነት ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር ከአሁኑ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመደርደር መሆኑን የገለጸው ፓርቲው፣ የአንድነት አመራሮችና አባላት በግፍ በማሰር ፓርቲው በምርጫው እንዳይሳተፍ ከፍተኛ የሆነ ጫና መደረጉን በዋቢነት አቅርቧል።
ኢህአዴግ ደጋፊዎቼ የሚላቸውን ብቻ በመራጭነት አስመዝግቦ ምርጫ የሚያደርግበት ሁኔታ እንዲያበቃ ደጋፊዎቻቸው በመራጭነት እንዲመዘገቡ ከማበረታት ጀምሮ የህዝብና የፓርቲ ታዛቢ በመሆን የምርጫ ሂደቱን በሙሉ በንቃት እንዲከታተሉ ጥረት እንደሚያደርግ አስታውቋል።
“የኢትዮጵያ ህዝብ በገዥው ቡድን መልካም ፍቃድ ወይም በማንኛውም ውጫዊ ተፅዕኖ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደማይሰፋ ሊገነዘብ ይገባል” የሚለው አንድነት፣  ምህዳሩ የሚሰፋውና ትክክለኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚኖረው ህዝቡ በጠቅላላ ከፍርሀት ቆፈን ተላቆ በሙሉ ልብ ለመብቱ ሲቆም፣ ለፓርቲዎች ተገቢውድጋፍ ሲሰጥ፤ ከፍ ሲልም ወደ ትግሉ ሲቀላቀል ነው” በማለት በአገር ውስጥና በውጭ ላሉ ኢትዮጵያውያን መልእክት አስተላልፏል። ፓርቲው ከህዳር 14 እስከ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚቆይ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ መጀመሩንም ገልጿል።
በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲን ያቀፈው የ8 ፓርቲዎች የጋራ መድረግ በኢትዮጵያ ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ቅድመ ሁኔታዎች አልተማሉም በሚል የአንድ ወር የትግል መርሃ ግብር ነድፈው በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው። ድርጅቶቹ ባለፈው እሁድ የጠሩት ስብሰባ በፖሊስ እንደተደናቀፈባቸው መዘገቡ ይታወሳል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ለነጻ ምርጫ የሚሆን ምቹ ሁኔታ የለም በሚል ምርጫውን እንደማይታዘብ እየገለጸ መሆኑን ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። በአለም የምርጫ ታዛቢ በታአማኒነቱና በስራ ጥራቱ ቀዳሚ የሚባለው የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን፣ የምርጫ 97 እና 2002 ምርጫዎችአለማቀፍ መስፈርትን እንደማያሟሉ መግለጹ ይታወሳል።

Friday 21 November 2014

ሰበር ዜና "የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ"

ሰበር ዜና

የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ
• ‹‹ማስጠንቀቂያውን እንደ ቁም ነገር አንቆጥረውም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
• ‹‹ስርዓቱ ምን ያህል ዝቅጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል›› አቶ ግርማ በቀለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረው የ9ኙ ፓርቲዎች የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ፀረ
 ህገ መንግስት በመሆኑና ነዋሪዎችን ሰላምና ፀጥታ በማወኩ በቀጣይ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ካደረገ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት 
ሲባል እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ፡፡

አስተዳደሩ ትናንት ህዳር 11/2007 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ፤ ህዳር 6 ቀን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል በሰማያዊ ፓርቲ 
አመራሮችና አባላት ለህዝብ የተሰራጨው በራሪ ወረቀት ህገ ወጥ መሆኑን፣ ህዳር 7/2007 ዓ.ም በኢንጅነር ይልቃል ጌትነት 
መሪነት ሊደረግ የነበረው አደባባይ ስብሰባ ህገ ወጥ እንደነበርና በወቅቱ የስብሰባው ተሳታፊዎች ከፖሊስ ጋር ግብ ግብ 
ከመግጠማቸውም በተጨማሪ የአካባቢውን ህዝብ ሰላምና ፀጥታ አውከዋል ሲል ከሷል፡፡ አስተዳደሩ አክሎም ፓርቲው 
የአደባባይ ብጥብጥና ሁከት በመፍጠሩ እርምጃ እወስዳሉ ሲል ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ልኳል፡፡



በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲ በቀን 5/3/2007 ዓ.ም ለአስተዳደሩ የእውቅና ደብዳቤ ያስገባ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የሰማያዊ 
ፓርቲና የትብብሩ አመራሮች አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ከገዥው ፓርቲ ፍርሃት የመነጨ በመሆኑ ከእንቅስቃሴያቸው 
እንደማይገታቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብርና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች 
ደብዳቤው ስርዓቱ የደረሰበትን መጠነ ሰፊ የፍርሃት ደረጃና ትግሉን ይበልጥ አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን የሚያሳይ ነው ሲሉ 
ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡




   
                                                                                                                                                                                                                                                                                               
ማስጠንቀቂው የደረሰው ሰማያዊ ፓርቲና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹የረዥም ጊዜ 
የመንግስት ታሪክ ባላት አገር የከተማ አስተዳደር ነኝ ያለ አካል እንዲህ አይነት ደብዳቤ መጻፉ ኢትዮጵያ ምን ያህል ውድቀት 
እንደገጠማትና እኛም እንደ ህዝብ የውረደት ካባ መከናነባችን በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ እንደ ሰማያዊ አሊያም የትብብሩ 
ሊቀመንበርነት ሳይሆን እንደ አንድ ይህን ያህል ውርደት እንደገጠማት አገር ዜጋ ሀፍረት ይሰማኛል፡፡›› ሲሉ አስተዳደሩ 
የላከው ደብዳቤ ላይ አስተያየታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂያው በቀጣይ የፓርቲውም ሆነ የትብብሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጣው ችግር ካለ በሚል ለኢንጅነር ይልቃል 

ላነሳነላቸው ጥያቄም ‹‹ደብዳቤው የኢህአዴግ ፍርሃት ገደብ መልቀቁንና ትግሉም ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት የሚያሳይ 
ነው፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ህዝባዊ እንቅስቃሴን ብቻ ሳይሆን የራሱን ጥላም አለማመን ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያል፡፡ እኛ 
ይህን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደቁም ነገር አንቆጥረውም፡፡ ይበልጡንም ለትግሉ በተጠናከረ መንገድ ንድንነሳሳ 
ይገፋፋናል›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የትብብሩ ፀኃፊና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ማስጠንቀቂያው 
ትብብሩ በየሳምንቱ ያቀዳቸውን መርሃ ግብሮች ለማደናቀፍ ያለመ ነው፡፡ ከአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲህ አይነት 
አሳፋሪ ደብዳቤ መጻፉ ስርዓቱ ምን ያህል ዝግጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል፡፡ ሆኖም ማስጠንቀቂያው ከእንቅስቃሴያችን 
አይገታንም፡፡ እንዲያውም ለዚህ የስርዓቱ ዝቅጠት የሚመጥን ስልት ነድፈን በጋራ እንድንሰራ ያደርገናል፡፡›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Thursday 20 November 2014

በእስር ላይ የሚገኙት ፖለቲከኞችና አክቲቪስቶች የዋስትና መብታቸውን ተከለከሉ

ኀዳር ፲፩(አስራ አንድቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-የአንድነት ፓርቲዎቹ ሃብታሙ አያሌውና ዳንኤል ሽበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲው የሽዋስ አሰፋ፣ የአረና ፓርቲው መምህር አብረሃ ደስታ እና ሌሎች 6 የመብት ተሟጋቾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።

በአቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ መዝገብ የተከሰሱት አስሩ ፖለቲከኞችና የመብት ተሟጋቾች፣ ህገመንግስቱን ጠቅሰው የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
ሁሉም እስረኞች በሽብር ወንጀል መከሰሳቸው ይታወቃል። አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ክሱ ከፖለቲካ ጋር የተያያዘ ነው በማለት ውድቅ ያደርጉታል። ፍርድ ቤት ለህዳር 17 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠጡም ታውቋል፤፡
በሌላ ዜና ደግሞ በትግራይ የታሰሩት ወጣት ሽሻይ አዘናው እና አማረ ተወልደ እስካሁን የታሰሩበት ቦታ አለመታወቁን አቶ አስገደ ገብረስላሴ ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ በህወሃት የደህንነት ሃይሎች ታፍነው ከተወሰዱ በሁዋላ የት እንደገቡ ባለመታወቁ፣ ከክልሉ ፕሬዚዳንት ጀምሮ ላሉ ባለስልጣናት አቤት ቢባልም መልስ የሚሰጥ መጥፋቱን አቶ አስገደ ገልጸዋል።
ኢህአዴግ ባለፈው ወር በተለያዩ ክልሎች ባደረገው አፈና በርካታ የዞንና የወረዳ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እየተያዙ ታስረዋል።በቅርቡ ከታሰሩት መካከል ዘነበ ሲሳይ፣ ጥላሁን አበበ፣ አግባው ሰጠኝ፣ ዘሪሁን ብሬ፣ ታስፋየ ታሪኩ፣ አንጋው ተገኝ፣ አባይ ዘውዱ ይገኙበታል።