Tuesday 26 May 2015

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!

EPPF-G7-header

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር

 May 25, 2015
ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።
ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።
የዘንድሮው ምርጫ 2007 ከዚህ በፊት ከነበሩ በባሰ ለአፈና የተጋለጠ የነበረ መሆኑ ከጅምሩ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነበር። በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ አገዛዙ የወሰደው የግፍ እርምጃ የዚሁ የምርጫ ዘረፋ ስትራቴጂ አካል ነበር። ከዚያ በተጨማሪም መራጮች እውነተኛ ፍላጎታቸውን በነፃነት መግለጽ እንይችሉ ዘርፈ ብዙ ጫናዎች ሲደረግባቸው ቆይቷል። የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላት እንደተፎካካሪ ሳይሆን እንደጠላት ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ ሰንብቷል። በምርጫው ሰሞንና በዕለቱ በተለይ ከተሞች በባዕድ ጦር የተወረሩ መስለው ነበር። ይህ ሁሉ ስነልቦናዊና አካላዊ ተጽዕኖ ታልፎ የተሰጠው ድምጽ ቆጣሪው ራሱ “ተወዳዳሪ ነኝ” ባዩ ህወሓት ነው።
በእንዲህ ዓይነት ምርጫ መሳተፍ ትርፉ “በሕዝብ ድምጽ ተመረጥኩ የማለትን እድል ለአምባገኑ ህወሓት መስጠት ነው”፤ “ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብም የተምታታ መልዕክት ማስተላለፍ ነው”፤ ”ለህወሓት ተጨማሪ ገንዘብ ማግኛና የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ ማራዘሚያ ነው“ በሚል በዚህ ምርጫ ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ አርበኞች ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በርካታ ወገኖቻችን የምርጫ ካርድ ቢያወጡም የደረሰባቸውን ጫና ተቋቁመው በምርጫው ባለመሳተፍ ላሳዩት ጽናት አርበኞች ግንቦት 7 አድናቆቱን ይገልፃል። 
ህወሓት በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ የምርጫ ጉዳይ እና የምርጫ ፓለቲካ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳን ተጨማሪ ማስረጃ ለሚፈልጉ ግንቦት 16 ቀን 2007 መጥቶላቸዋል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ጥያቄ የሚከተለው ነው – አገራችን ከህወሓት አፈና ነፃ ለማውጣት ያለን አማራጭ መንገድ ምንድነው
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህወሓት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ የሚወርደው ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽን ባቀናጀ ሁሉገብ ትግል ነው ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ለሁለቱም የትግል ዘርፎች ተስማሚ የሆኑ አደረጃጀቶችን አዘጋጅቷል።
ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ታጋዩ ከመኖርያ ወይም ከሥራ ቦታው ሳይለቅ በህቡዕ የሚከናወን ትግል ነው። ሕዝባዊ አመጽ ደግሞ ከመኖሪያና ሥራ ቦታ ለቆ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች የህወሓትን ህጎች በመቃወም የሚደረጉ ናቸው። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች ድርጅት፣ ዲሲሊንና ጽናትን ይጠይቃሉ። ለድላችን ሁለቱም የትግል ዘርፎች እኩል ዋጋ አላቸው። እናም ከዛሬ ጀምሮ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባለውና አቅሙ በሚመቸው የትግል ዘርፍ ይሳተፍ። ሕዝባዊ ኃይልን መቀላቀል የቻለ ይቀላቀል፤ ያልቻለው በያለበት ተደራጅቶ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ይታገል።
በየመኖሪያ ሠፈሩና በሥራ ቦታዎች የሚቋቋሙ የአርበኞች ግንቦት 7 ማኅበራት በርካታ ሥራዎች አሏቸው። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅትን ማጠናከር የሁላችንም ድርሻ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም፤ እናም ትኩረታችን እዚያ ላይ እናድርግ። እያንዳንዳችን ከሚመስሉንና ከምናምናቸው ጋር ተነጋግረን እንደራጅ፤ ወያኔ የሸረሸረብንን በራስ መተማመን እና የእርስ በርስ መተማመንን መልሰን እንገንባ። ውስጥ ውስጡን ጠንካራ አገራዊ ኅብረት እንፍጠር፤ የዕለት ተዕለት ተግባሮቻችን ደግሞ አካባቢያዊ ይሁኑ። ድርጅታችንን እያጠናከርን ወያኔን ከሁሉም አቅጣጫ እንሸርሽረው እንገዝግዘው። በዚህ መንገድ በሚደረግ ሕዝባዊ ትግል የሚገኝ ድል ፈጣን ከመሆኑን በላይ የድሉ ሕዝባዊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ይሆናል።
ስለሆነም እያንዳንዱ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ታጥቆ እንዲነሳ፤ ወደ ተግባራዊ ትግል ፊቱን እንዲያዞር አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Friday 22 May 2015

UN investigates Briton on death row in Ethiopia

UN investigates Briton on death row in Ethiopia
Special rapporteur on torture asks UK and Ethiopian governments about detention 
of Andargachew Tsige amid claims of ill-treatment
The detention of a British citizen held on death row in Ethiopia for almost a year is being 
investigated by the United Nations official responsible for preventing torture.
Andargachew Tsige was arrested last June while in transit through Yemen’s main airport 
and forcibly removed to Addis Ababa. He is the leader of an opposition party and had been 
condemned to death several years earlier in his absence.
uan Mendez, the UN special rapporteur on torture, has written to the Ethiopian and UK 
governments saying he is investigating the treatment of Tsige. There are claims Tsige is 
being deprived of sleep and held in isolation.






His partner, Yemi Hailemariam, also a British national, who lives in London with their three 
children, said she had only spoken to him once by telephone since his abduction. “He’s in 
prison but we have no idea where he is being held,” she said. “He said he was OK but I’m 
sure the call was being listened to.
“He had been in Dubai and was flying on to Eritrea when the plane stopped over in Yemen. 
He hadn’t even been through immigration. We think Yemeni security took him and handed 
him over to the Ethiopians.
“They say there was an extradition agreement but it was so quick there was no time for any 
semblance of a legal hearing. Yemen and Ethiopia had close relations then. The [Ethiopian] 
government have put him on television three times in heavily edited interviews, saying he 
was revealing secrets

“He has been kept under artificial light 24 hours a day and no one [other than the UK 
ambassador] has had access to him. I feel angry with the Foreign Office. They know they 
could do more. They have political leverage they could use but have not done so.”
Tsige, 60, known as Andy, had previously been secretary general of Ginbot 7, a political 
opposition party that called for democracy, free elections and civil rights. He first came to 
the UK in 1979. The Ethiopian government has accused him of being a terrorist. In 2009, 
he was tried with others in his absence and sentenced to death.
No effort was made to extradite him to face the court. A US embassy cable, released 
through WikiLeaks, described the trial as “lacking in basic elements of due process”.
“[Andy] is a politician, not a terrorist,” said Hailemariam. “It’s just the Ethiopian government 
that thinks it does not need to make any space for the opposition. A delegation of British 
MPs, including Jeremy Corbyn, were stopped from travelling to Ethiopia in February. They 
are hoping to try again.”
Hailemariam’s dissatisfaction with the UK government’s response follows the release of 
internal Foreign Office memorandums earlier this year that appeared to show official 
reluctance to apply pressure on Ethiopia to obtain Tsige’s release.
The UK prime minister, David Cameron, has, however, written a letter to his Ethiopian 
counterpart, Hailemariam Desalegn, raising concerns about Tsige.
A Foreign Office spokesman said: “The foreign secretary has raised this case with the 
Ethiopian foreign minister on 13 separate occasions. We will continue to lobby at all levels, 
conveying our concern over Andargachew Tsige being detained without regular consular 
visits and access to a lawyer.”
Maya Foa, director of Reprieve’s death penalty team said: “Andy Tsige was illegally 
kidnapped and rendered to Ethiopia, where he has now been held in a secret location for 
nearly a year. The UN special rapporteur is right to raise concerns about torture – 
especially given Ethiopia’s terrible record on human rights, and their denial of any 
meaningful consular access.
“It is crucial that the British government now takes stronger action on this case. The way 
Andy has been treated is in serious violation of international law and the most basic 
principles of justice – the UK must push for his immediate release.”
Tsige’s lawyer, the barrister Ben Cooper of Doughty Street chambers, said: “[He] was 
abducted at an international airport, hooded and rendered to Ethiopia, where he has been 
held incommunicado under a death sentence that was passed unlawfully in his absence. 
He remains in isolation nearly a year later with only occasional access to the open air.
“His detention violates all minimum standards of treatment. We ask the Foreign Office to 
follow the lead of the UN special rapporteur on torture to demand an immediate end to Mr 
Tsege’s torture by seeking his return home to his family in England. This is a clear case of 
kidnap and should be treated as such.”
Elections are taking place in Ethiopia this weekend. Tsige’s family hopes the government 
will relax restrictions on the opposition once voting is over.
In a lengthy statement, the Ethiopian embassy said that Ginbot 7 had been proscribed a 
terrorist organisation by the country’s parliament. Tsige, as general secretary, it added, was 
charged with “conspiring to perpetrate terror and violence in Ethiopia by planning, training, 
financing, and organising terrorist recruits in Eritrea” and found guilty of “conspiring and 
working with and under Ginbot 7, to overthrow the legitimate government of Ethiopia 
through terrorist acts”.
Following conviction and sentence, the embassy continued, the government sent a formal 
request of assistance to those states with which Ethiopia has an extradition treaty, 
requesting them to transfer all sentenced individuals in the event of their presence on their 
territory.
“It was on the basis of this request, and the existing extradition treaty with the Republic of 
Yemen, that [he] was extradited to Ethiopia. Accordingly, [he] is currently in detention at the 
federal prison,” it said.
The statement added: “Mr Tsige was serving as a Trojan horse, assisting the Eritrean 
government’s repeated and ongoing attempts to wreak havoc and instability in the sub-
region. Mr Tsige is well-treated and has received visits from the British ambassador to 
Ethiopia. He has also spoken to his family on the phone.”

የወያኔን የይስሙላ ምርጫ አስመልክቶ ከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈ ጥሪ

May 22, 2015
የተከበራችሁ እናቶቼና አባቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ እንዲሁም ልጆቼ የምትሆኑ ወጣቶች!!
dr-berhanu-Nega
አገራችን የምትገኝበትን አስጨናቂ ሁኔታ ሁላችንም እንረዳለን። የህወሓት/ኢሕአዴግ ፋሽስቶች ቡድን እየገረፈ፣ እያሰረና እየገደለ በካርዳችሁ መርጣችሁ የምርጫ ድግሴን ካላሞቃችሁልኝ እያለ ነው። እንኳንስ ዛሬ ታዛቢ በሌለበት፤ ታዛቢ እያለም እንኳን ወያኔ የሕዝብን ድምጽ በትክክል ቆጥሮ አያውቅም። ወያኔ ለህዝብ ድምጽ ምንም ደንታ የሌለው የኋላቀር ወሮበሎች ቡድን ነው::

ለስንት አስርት ዓመታት ለወያኔ ባርነት እንገብራለን? ለሀያ አስምስት ዓመታት ተገዛን፣ ተገደልን፣ ተቀጠቀጥን፣ ታሰርን፣ ተሰቃየን፣ ልጆቻችን በአገራቸው ተስፋ ቆርጠው ሲሰደዱ በበረሀ ንዳድ አለቁ፤ በባህር ሰጥመው ቀሩ፤ በባዕዳን አረመኔዎች እንደከብት ታረዱ፤ ቤንዚን ተርከፍክፎባቸው ተቃጠሉ። ሀይማኖታችን ተዋረደ፤ ባህላችን ረከሰ፤ ታሪካችን ተናቀ። በልማት ስም ወልደን ከከበድንበት ተፈናቀልን፤ አገራችን አደገች እያለ ሕዝብ በኑሮ ውድነት ተሰቃየ። በልቶ ማደር ብርቅ ነው። እንደሙጫ የሚያጣብቀንን ማህበረሰባዊ ትስስር በስልጣን ለመቆየትና ህብረተሰቡን ለመዝረፍ ሲል ሆን ብሎ እያፈራረሰው ነው:: ይኽ ሁሉ አይበቃንምን? ይኸ ሁሉ አይመረንምን?
ወላጆቼ፣ እህት ወንድሞቼ!ውርደት ይብቃን። የተረገጥንና የተገደልን አንሶን ፍጹም ማንንም ሊያሞኝ በማይችል የለበጣ ምርጫ ወደን የተረገጥን፤ ፈልገን የተገዛን ለማስመሰል ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እናክሽፈው:: ከፊታችን ያለውን ምርጫ ባለመሳተፍ ምሬታችንን እንግለጽ።
ዛሬ በግሌ እና በአርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ። በዚህ ምርጫ አትሳተፉ። የምርጫ ካርዳችሁን ቀዳችሁ ጣሉት። እናምርር። ካላመረርን ለውጥ ሊመጣ አይችልም። ይልቅስ ለማይቀረው የመጨረሻው ትግል ራሳችንን እናዘጋጅ::
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሞ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር ትብብር በመፍጠር የአገር አድን ኃይል በመገንባት ላይ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት አንከፋፈልም። ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ያካተተ ስብስብ ፈጥረን በኅብረት አገዛዙን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ትግል ነው። የትግሉም ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው። ክርስቲያን ሙስሊም፤ ወንድ ሴት፤ ወጣት አረጋዊ ሳንል፤ በብሔርም ሆና በቋንቋ ሳንከፋፈል ሁላችንም ይህን አስከፊ ሥርዓት በቃህ እንበለው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ይህንን የውሸት ምርጫ ባለመሳተፍ ለለውጥ ያለህን ዝግጁነት አሳይ! ደግሜ እለዋለሁ – የምርጫ ካርድህን ቅደድ!!!
የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!
እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። በወገኖቻችሁ ላይ አትተኩሱ። ይልቁንስ አፈሙዛችሁን አገራችንን ለውርደት በዳረገውና በሙስና በተጨማለቀው ዘራፊው የህወሓት አገዛዝ ላይ አዙሩት። ታሪካችሁን ከምታበላሹ፤ ታሪክ ሥሩ። ለራሳችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁ፣ ለልጆቻችሁ እና ለሕዝብ የሚጠቅም አገርና መንግሥት እንዲኖረን የእናንተ የግልም ሆነ የጋራ ተነሳሽነት ወሳኝ ነው። ወያኔ ህዝቡን የሚዘርፈው በእናንተ ትከሻ ላይ ቆሞ እንደሆነ ላንዳፍታም አትርሱት:: እንደመላው ህብረተሰብ እናንተም በነጻነትና በኩራት የምትኖሩበት ሀገር እንደምትሹ አልጠራጠርም:: ስለዚህም ይህን የህወሓት የውሸት ምርጫ ተቃወሙ። ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ ትግላችን እስከ ነፃነት ድረስ ይቀጥላል። ነፃነታችንን በእርግጠኝነት በትግላችን እንቀዳጃለን። የምትወዷት፣ የምትኮሩባት አገር – ኢትዮጵያ – ትኖረናለች። ለዚህ ግን ዛሬ ተደራጅተን፣ ፀንተን መታገል የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ዛሬ ሁላችንም በፍላጎትና በመንፈስ የተገናኘን ነንና ሁሉም በያለበት ትግሉን ያጧጡፍ። ውጤቱ ቀድሞ በታወቀው በዚህ ምርጫ አለመሳተፍ ለትግሉ ያለንን ቁርጠኝነት ማሳያ ነውና ለውሸት ምርጫ ያለን የመረረ ተቃውሞ በምርጫው ባለመሳተፍ እናሳይ።
ነፃ እንወጣለን!
የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱ ባለቤት ይሆናል!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Tuesday 12 May 2015

የቀድሞ የመኢአድ የሕዝብ የህዝብ ግኑኙነት ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች ኤርትራ ለትጥቅ ትግል መግባታቸውን ገለጹ

Hiber Radio 

 ፣<<ወያኔን በሰላማዊ ትግል አይወድቅም ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ በትጥቅ ትግል መታገል ነው>>
ወጣት ተስፋሁን አለምነህ 
የቀድሞ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው ወጣት ተስፋሁን አለምነህ በአገር ቤት የወያኔን አገዛዝ በሰላማዊ ትግል ታግሎ መጣል አይቻልም ብሎ በመወሰን እሱና ሌላው የመኢአድ አባል ደሳለኝ ሲሳይ ከበርካታ ወጣቶች ጋር ኤርትራ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ሰሞኑን መግባታቸውን ለህብር ሬዲዮ ከስፍራው በሰጠው አጠር ያለ ቃለ ምልልስ ገለጸ።

<በአስቸጋሪ ሁኔታ አልፈን የቀድሞው መኢአድ ግማሹ ክንፍ ኤርትራ ገብተናል>> በሚል አርዕስት ለህብር የላከውን ማስታወሻ እውነተኛነት ለማጣራት ባቀረብነው ጥያቄ የኤርትራ ስልኩን ልኮልን እሱም ሆነ ሌሎቹ በትጥቅ ትግል ስርዓቱን ለመጣል ኤርትራ የገቡ ወጣቶች መኖራቸውንና  ገልጿል ።
በአገር ቤት በሰላማዊ ትግዩ አምንን በተደጋጋሚ ስንታሰርና መከራ ሲደርስብን ነበር ያለው ተስፋሁን ሰላማዊ ትግሉ መሪያችን ፕሮፌሰር አስራትን ጨምሮ ብዙዎችን ከማስበላት ያለፈ ስርዓቱን ለማዳከም ባለመቻሉ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ኤርትራ መግባታቸውን አረጋግጦልናል ።
<<ወያኔን በሰላማዊ ትግል አይወድቅም ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ በትጥቅ ትግል መታገል ነው>> ያለው ወጣት ተስፋሁን አለምነህ ስርኣቱን በሰላማዊ መንገድ ብቻ ታግሎ መጣል አለመቻሉን ጠቅሷል።
ከወጣት ተስፋሁን አለምንህ ጋር ያደረግነውን አጠር ያለ ቃለ ምልልስ ዘግይተን እናቀርባለን።
http://www.hiberradio.com/archives/500

Saturday 9 May 2015

”ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው” – ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

April 24, 2015
የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ 
ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ
Berhanu Interviewየተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም

የቁልቁለቱን ጉዞ እናስቁም፤ ውርደት ይብቃን!!!

May 6, 2015
def-thumb
የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።

አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።
ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተያዙበት ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተባለ


ሚያዝያ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በከፍተኛ ህመም በመሰቃየት ላይ ሲሆኑ እስካሁን በዶክተሮች ለመጎብኘት አልቻሉም።

አያያያዛቸው የከፋ መሆኑን በማስመልከት የእንግሊዝ መንግስት አስቸኳይ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መጻፉንም ምንጮቻችን ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ያለፉትን ተከታታይ ወራት ጸሃይ የሚባል ነገር ሳያዩ ጨለማ ቤት ተዘግቶባቸው አሳልፈዋል; ከህመማቸው ጋር በተያያዘም ምግብ መመገብ በእጅጉ ቀንሰዋል።
በከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው፣ አያያዛቸው አስከፊ እንደሆነ በቅርቡ ለጎበኙዋቸው የእንግሊዝ አምባሳደር መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ይህንን ተከትሎም የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጠንከር ያለ ደብዳቤ መጻፉን የአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ በአፋጣኝ የማይለወጥ ከሆነ፣ በህይወታቸው ላይ ያልተጠበቀ አደጋ ሊፈጠር እንደሚችል ያስጠነቀቁት የእንግሊዝ ባለስልጣናት፣ አቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር ድጋፍ እንዲያገኙ፣ በመደበኛ እስር ቤት ውስጥ እንዲታሰሩና በጠያቂዎች እንዲጎበኙ ፣ ሃኪሞች እንዲያዩዋቸውና ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ደብዳቤ መጻፋቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ገዢው ፓርቲ ከአቶ አንዳርጋቸው የረባ መረጃ ለማግኘት ባለመቻሉ_የስነ ልቦና ጫና በማሳረፍና ህክምና በመከልከል ለመጉዳት ማሳቡን ምንጮች ገልጸዋል።
የእንግሊዝ ባለስልጣናት በሂደት ስለሚወስዱት እርምጃ ግልጽ ባያደርጉም፣ ጉዳዩን በቀላሉ እንደማያዩት ለኢህአዴግ ሹሞች እንደገለጹላቸው ታውቋል።
አቶ አንዳርጋቸው በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ለኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች ተላልፈው ከተሰጡ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ሁለት ጊዜ በቴሌቪዥን አቅርቧቸዋል። ተቆራርጦ የተላለፈውን ቪዲዮ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ትችት ሲቀርብብት ቆይቷል።
ኢህአዴግ አቶ አንዳርጋቸውን ህዝብ ሊጎበኛቸው በሚችል እስር ቤት አለማሰሩና ሰብአዊ መብታቸውን ሁሉ መግፈፉ የገዢውን ፓርቲ የፍርሃትና የበቀል ደረጃ፣ እንዲሁም ራሱ ላወጣው ህግ እንኳን የማይገዛ መሆኑን የሚያሳይ ነው ተብሏል።

የግብጹን መሪ ሰብአዊነት ያዩ ባለ ሥልጣኖች ለሕዝባቸው ምን ምላሽ አላቸው?!

May 8, 2015
በፍቅር
ብጥብጥና ኹከት በነገሠባት፣ እንደ አይ ኤስ ላሉ ጽንፈኞች፣ አክራሪ፣ ጨካኝና ነፍሰ ገዳይ ቡድን መናኻሪያ ከኾነችው ከአገረ ሊቢያ ባለፈው ሰሞን ኹላችንንም እጅጉን ያሳቀቀን፣ እንባን ያራጨን፣ እማማ ኢትዮጵያን የኀዘን ከል ያለበሰ ከፉ መርዶን፣ የሚሰቀጥጥ ዜናን ሰምተናል፡፡ እንባችን ገና ከዓይናችን ሳይደርቅና ሳይታበስም ደግሞ ከዛች የሞት ምድር በምንሰማው ወገኖቻችን የእባካችሁ የድረሱልን ጥሪ ግራ ተጋብተን፣ በምናምጥበት፣ እግዚኦ አምላክ ሆይ ድረስልን! እያልን ባለንበት ከፈርዖኖቹ ምድር፣ ከዓባይ ስጦታ ምድር፣ ከወደ ግብጽ ደስ የሚያሰኝ የምሥራችን ሰማን፡፡
President Sisi (L) receiving Ethiopians who were freed by Egypt's security services
President Sisi (L) receiving Ethiopians who were freed by Egypt’s security services
ከመሐመድ ጋዳፊ ሞት በኋላ ይኼ ነው የሚባል መሪ በሌላት በአገረ-ሊቢያ በስደት፣ በሞት ፍርሃትና በሥጋት ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን የግብጽ መንግሥት ነጻ አውጥቷቸው በዛች በፈርኦኖች ምድር ወገኖቻችን ደስታቸውን ሲገልጹ ዐየን፡፡ ለእነዚህ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የአገሪቱ ፕሬዝዳንት የኾኑት ጄ/ል አብዱልፈታህ አል ሲሲ በዓለም አቀፉ በካይሮ አየር ማረፊያ ከባለ ሥልጣኖቻቸው ጋር በአካል ተገኝተውም አቀባበል ሲያደርጉላቸው ጭምርም፡፡
ኢትዮጵያውያኑም ስደተኞች ፊታቸው ላይ አንዳንች ልዩ ስሜትና ፈገግታ እየተነበባቸው የግብጽን ባንዲራ እያውለበለቡ ከሞት ሥጋትና ፍርሃት ላታደጓቸው የግብጽ መንግሥትና ለጄ/ል አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አድናቆታቸውን፣ ምስጋናቸውን ሲገልጹ የሚያሣዩ ምስሎችንና ቪዲዮዎችንም በርካታ ኢትዮጵያውያን በአድናቆትና እጅግ በመገረም በማኅበራዊ ድረ ገጾች እየተቀባበሉት ይገኛሉ፡፡
በርካታዎችም፡- ‹‹ከናዝሬት መልካም ነገር ይወጣልን?! እንዲል ቅዱስ መጽሐፍ በታሪካዊ ጠላትነት ከፈረጅናት ከግብጽ ይሄ ዓይነቱ መልካምነት፣ ደግነት እንዴት ኾነ በሚል በመንታ ስሜት ውስጥ ኾነው የግብጽን መንግሥት በእጅጉ እያመሰገኑ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ ከምስጋናቸው ባሻገር ይህ የጄ/ል አል-ሲሲ ዕርምጃ አንዳች ፖለቲካዊ አጀንዳና ዲፕሎማሲያዊ መልእክት እንዳለው እየተናገሩ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደታች ጥቂት ነገሮች አነሣለሁ፡፡ ለነገሩ ይኼ ሁለተኛ ነገር ይመስለኛል፡፡ ትልቁና ዋናው ወገኖቻችን በሕይወት ለአገራቸው ምድር የሚበቁበት መንገድ መመቻቸት መቻሉ ነው፡፡
ዛሬ በሊቢያ በረኻ የወገን፣ የመንግሥት ያለኽ! በሚል ሲጮኹና ሲንከራተቱ የነበሩ እነዚህ ወገኖቻችን ከጭንቀትና ከሥጋት ተገላግለው የሰላም አየር ወደሚተነፍሱበት ወደ ግብጽ ምድር በሰላም መድረሳቸው ሰው የመኾን ክብርን፣ ፍቅርና ሰብአዊ ርኅራኄ ምን እንደኾነ በቅጡ ለምንረዳ ሰው ለኾንን ሰዎች ኹሉ ከፖለቲካውም፣ ከዲፕሎማሲያዊውም አጀንዳ በላይ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፣ የሚገባኝም!!
በእርግጥም እነዚህ ወገኖቻችን ከዛ የሞት መናፍስት ካረበቡበት፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ የሞት አበጋዞችና የክፋት ልጆች ያለ አንዳንች ከልካይ የጥፋት ሰይፋቸውን መዘው ከሚርመሰመሱበት፣ ሞትና ጭካኔ ከነገሠባት ከምድረ ሊቢያ ነጻ ወጥተው በሰላም ወደ ግብጽ ምድር መድረሳቸው እፎይ፣ ተመስገን ፈጣሪ ሆይ የሚያሰኝ ታላቅ ነገር፣ ድንቅ የኾነ የምስራችም ነው፡፡ ሌሎችም በጣርና በጭንቅ ያሉ ወገኖቻችንም የእነርሱ ዕድል እንዲገጥማቸው ነው የምንጸልየው፣ የምንመኝላቸው፡፡
እንደ እውነቱ ከኾነ ኢትዮጵያውያኑ በካይሮ አየር መንገድ የግብጽን ባንዲራ እያውለበለቡ ከመከራ፣ ከጭንቀት፣ ከሞት ለታደጋቸው የግብጽ መንግሥት ደስታቸውን ሲገልጹ ማየት በሥልጣን ላይ ላለው የኢሕአዴግ መንግሥት ትልቅ ኪሣራና ውርደት ነው፡፡ በነጋ ጠባ ልማት፣ ዕድገት እያለ የሚለፍፈው መንግሥት ሕዝቡን ከስደት ለመታደግ አቅቶትና ያለ ምንም እፍረት የወገኖቻችንን እልቂት ለራሱ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሲጠቀምበት ታዝበነዋል፡፡ ይህን ውርደት ከማየት የበለጠ እንደ አገር፣ እንደ ሕዝብ ምን የሚያሳፍር፣ ምን የሚጠዘጥዝ ሕመምና ሥቃይ ይኖራል ወገን፡፡
እንደው የጄ/ል አል ሲሲ ምንም የተደበቀ ይባል የተሰወረ ፖለቲካዊ/ዲፖሎማሲያዊ አጀንዳ ይኑራቸው ግና ኢትዮጵያውያኑ ወገኖቻችንን በካይሮ አየር መንገድ ማረፊያ ገኝተው አቀባበል ሲያደርጉላቸው፣ የወገኖቻችንን በግፍ መታረድ ሰምተው ቢያንስ እንኳን ለሕዝቡ መጽናኛ የሚሆን መልእክት ለማስተላለፍ እንኳን ገና እያጣራን ነው በሚል በወገኖቻችን ሞት ላይ ሰብአዊ ርኅራኄ በጎደለው ሁኔታ ርካሽ ፖለቲካቸውን ሲሸቅጡብን፣ ሲነግዱብን አንዳንች እፍረት ብሎ ነገር ያልተሰማቸው ባለ ሥልጣኖቻችን እንደው ይሄን የጄ/ል አል ሲሲን ደግ ተግባር ሲያዩ ምን ተሰምቶአቸው ይኾን?!
ከትልቅ አክብሮትና ትሕትና ጋር፣ ለመሆኑ ክርስቲያን ነን በሚል በአደባባይ ያወጁልን የአገራችን ርዕሰ ብሔርና ጠቅላይ ሚ/ር እነዚህን ወገኖቻችንን የግብጹ ፕ/ት ዓላማቸው ምንም ይሁን ምንም ካይሮ አየር ማረፊያ ድረስ ተገኝተው አቀባባል ሲደርጉላቸው ሲያዩ ምን ተሰምቶአቸው ይሆን?! መቼም ለወገናቸው ልባቸው ውስጥ የቀረች ትንሽ እንጥፍጣፊ የኾነች ፍቅር፣ ክብርና ሰብአዊነት ካላቸው ይህን ውርደትና እፍረት የሚሸከሙበት ጫንቃ፣ ወኔ ይኖራቸውስ ይኾንን?!
ከሊቢያ በረኻ እስከ ደቡብ አፍሪካ፣ ከየመን እስከ ሳውዲና መካከለኛው ምሥራቅ የወገኖቻችን ደም የውሻ ደም ያኽል እንኳን ክብር ተንፍጎት፣ ሕዝባችን ላይ የሞት ሞትና ውርደት ሲታወጅባቸው ኀዘናችን፣ ቁጭታችንን ብሶታችንን ለመካፈል አንድ ቀን እንኳን በቅጡ ድምጻቸው ያልተሰማው ባለ ሥልጣኖቻችን፣ መሪዎቻችን ይህን የአል ሲሲን ሰብአዊነት ሲመለከቱ ምን ተሰምቶአቸው ይኾን?! እናስተዳድረዋለን ለሚሉት ሕዝባቸው ፍቅርና ሰብአዊነት ብሎ ነገር የተራቆቱ እነዚህ ባለ ሥልጣኖቻችን ከበቀልና ከክፋት ወጥተው ቆም ብለው ልባቸውን፣ ራሳቸውን በቅጡ ይፈትሹ፡፡
ጭካኔና በቀል በረበበትና በሚነበብበት ፊታቸው፣ ወዳጃችን ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እንደጸፈው ማዘናቸውንም ኾነ መደሰታቸውን በማይገልጽ ድርቅ ያለ ስሜት፣ ከሥልጣን/ከወንበር ጋር ፍቅር በወደቀ ብኩን ልባቸው፣ በስንት ጉትጎታና እግዚኦታ በቴሌቪዥን ቀርበው የሚናገሩት ቃላቸው ሣይቀር እንደ በቆሎ ቂጣ አፋቸው ላይ እየተፈረፈረ ሲወድቅ እየታዘብን፣ ውስጣችን በኀዘን ነዶና ተኮራምቶ ከበገነ፣ ከተቃጠለ በኋላ የማታ ማታ የግዳቸውን የሚያስተላልፉልን እንጨት እንጨት የሚል ማጽናኛቸው እንኳን ከልባችን ከጆሮአችን ለመድረስ አቅም የሌለው መኾኑን ማን በነገራቸው፡፡
ለመሆኑ መንግሥታችን ፍቅርና ሰብአዊነት ምን እንደሆነ ይገባዋል፣ ያውቃልን?! እስቲ ከሰማችሁን ይህችን ዘመን አይሽሬ የኾነች ‹‹ታላቁ ነፍስ›› በሚል በሕዝባቸው የሚሞካሹት፣ የህንድ የነጻነት አባት የኾኑት ማሕተመ ጋንዲ በአንድ ወቅት ተናገሩትን አባባላቸውን ልጥቀስላችሁ፡- ‹‹Power based on Love is a thousand times more effective and permanent than power derived from fear.››
ፍርሃት አምጦ የወለደውን ጭካኔያችሁን እስቲ በፍቅር፣ በሰብአዊነትና በርኅራኄ ዘይት አለስልሱት፡፡ እንዲህ የምታስጨንቁትን ሕዝብ የሚያይ፣ የሚመለከት ፈጣሪ፣ ታዳጊ አምላክ እንዳለም አትዘንጉ፡፡ ያን አፍሪካን ሳይቀር የሚጠብቅ ግዙፍ የኾነ ሰራዊትና መሳሪያ ገንብቻለኹ፣ ማን ወንድ፣ የትኛውስ ጀግና ነው ከፊቴ የሚቆመው ብሎ የተገደረውን ደርግን/ጎልያድን በእናንተ በታናናሾቹ/በዳዊቶቹ ያዋረደው ሕያው አምላክ ዛሬም በዙፋኑ ላይ እንዳለ አትዘንጉት፡፡
እናም መሪዎቻችን ፍቅር ከምንም በላይ ኹሉን ለመግዛት፣ ኹሉን ለማሸነፍ የሚያስችል ታላቅ ኃይልና ብርቱ ጉልበት እንዳለው ቢረዱ እንዴት መልካም በኾነ ነበር፡፡ መሳሪያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ሠራዊታቸውን ተማምነው ሕዝቡን እያስጨነቀ፣ በምስኪን ሕዝቡ ላይ የብረቱን ቀንበር እያጠበቀ ላለው መንግሥታችን ይህ መልእክት ይድርሰው ዘንድ ምኞቴ ነው፡፡
እባካችሁ አምባ ገነኖች የሕዝብን ቁጣና ብሶት በኃይል፣ በመሳሪያ መግታት እንደማይቻልም ከታሪክ ተማሩ፡፡ እኛ ግን እንዲህ እንላለን፣ እንዲህም እንመኛለን፣ መቼም ምኞት አይከለከልምና፡-
ለሕዝብ የአደራ ቃል ታማኝ የኾኑ፣ በሕዝብ ፍቅር የነደዱ፣ በሕዝባቸው ጽኑ ቃል ኪዳን የታሰሩ፣ ራሳቸውን ለመሥዋዕትነት ያዘጋጁ እንደ አይሁዳዊው ሕዝብ ነጻ አውጪ እንደ ሙሴ፡-‹‹ይህን ሕዝብን በምድረ በዳ ከምታጠፋው እኔ ከሕይወት መዝገብ ደምስሰኝ፡፡›› የሚሉ፣ በሕዝባቸው ስለ ሕዝባቸው ፍቅር በነፍሳቸው የቆረጡ፣ ጽኑ፣ ባለ ራእይ የኾኑ፣ ከሥልጣን፣ ከወንበር በፊት ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ስፍራን፣ ክብርን ያገኙ፣ ጀግና መሪዎችን እንመኛለን፤ በእውነት ይህን ማግኘትም ትልቅ መታደል ነው፡፡
እንደ መውጫ ከፍጥረት ታሪክ ማግሥት ጀምሮ የግብጽ ምድር በረከት፣ ሲሳይና ሕይወት በኾነው በዓባይ ውኃ ሺ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸው ኢትዮጵያና ግብጽ፣ እስከ ዛሬ ዓይንና ናጫ ከኾኑበት የዓባይ ውኃ ፖለቲካ እስጥ አገባ ለጊዜውም ቢሆን ግብጾቹ አቋማቸውን አለሳልሰው እንዲያ እንዳላልናቁንና እንዳላዋረዱን፣ እንዲህ ወገኖቻችንን ከመታደግ ባለፈ በአደባባይ በርዕሰ ብሔራቸው አማካኝነት ወገኖቻችንን በክብር ለመቀበል የቻሉበት አካኼድ በኢትዮጵያና በግብጽ በኩል ለተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ ድርድር አንድ እመርታ፣ አንድ ታላቅ ድል እንደኾነ ነው የሚሰማኝ፡፡
ትንግረተኛ በኾነው በዓባይ ወንዛችን ምክንያት ጠላትነትን ከተርፍንባቸው ከግብጾቹ እንዲህ ዓይነቱ ሰብአዊነትና ርኅራኄ ማየታችን የግብጹን ፕሬዝዳንት እናመስግናቸው ዘንድ ያስገድደናል፡፡ በመንግሥታችን፣ በባለ ስልጣነሞቻችን እያፈርንና እየተሳቀቅንም ቢሆን በሂደት ግብጾቹ አቋማቸውን በማለሳለስ እንዲህ ዓይነቱን ወገኖቻችንን ከሞት የታደጉበትን የወዳጅነት ውለታቸውን፣ ሰብአዊ ርኅራኄያቸውን መቼውንም ቢሆን አገራችንና ሕዝባችን የሚረሳው፣ የሚዘነጋው አይሆንም፡፡
ግብጻውያኑ ከበዛው ተንኮላቸውና መሰሪነታቸው ጋርም ቢሆን ፈረንጆቹ፡- ‹‹A friend in need is a friend in deed!›› እንዲሉ በዚህ የእማማ ኢትዮጵያ ዋይታና የሰቆቃ የቀውጢ ጊዜ ቢያነስ ከጎናችን ቆመው ታማኝነታቸውንና ወዳጅነታቸውን አሳይተውናልና ልናከብራቸቀው፣ ልናወድሳቸው ግድ ይለናል፡፡
በሌላ በኩል ግን ከላይ ለመግለጽ እንደ ሞከርኩት ይህ የግብጽ መንግሥት ዕርምጃ ሕዝቡን ከስደት፣ ከባዕድ ጋር ከሚደርስበት ግፍ፣ መከራ፣ ሥቃይና ሞት ለመታደግ ወኔውም ኾነ አቅሙ ላነሰው፣ ለሚያስተዳድረው ለሕዝቡ ፍቅርና ክብር ለመስጠት ላዳገተው መንግሥታችን ግን ቢያስተውለው ታላቅ ውርደት፣ ኪሳራም ነው!!
የቀሩትም በስደት ላይ ያሉ ወገኖቻችን ወደ አገራቸው በሰላም ይገቡ ዘንድ ጸሎታችን ነው!! ‹‹እግዚአብሔር ትዕግሥትን፣ በጎ ትምህርትንም ይሰጣቸው ዘንድ የድካማቸውንም ፍጹም ዋጋ ይሰጣቸው ዘንድ ስለ ተሰደዱ ሰዎች እንማልዳለን፡፡›› እንድትል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ-ቅዳሴዋ!!
ሻሎም!!

Tuesday 5 May 2015

ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባና የገቢ ማሰባሰቢ በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ ተካሄደ!!

ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት በኢትዮጵያ ያለውን አፋኝ ዘረኛ የወያኔ አገዛዝን ለማስወገድ የሚደረገውን የሁለገብ ትግል ለመርዳትና አሁን ሀገራችን ያለችበትን አስከፊ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለመምከር እ.ኤ.አ  አፕሪል 18, 2015 የተዘጋጀው ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ኃላፊ የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ እና የኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም እንዲሁም ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች በመጡ በርካታ ታዳሚዎች በተገኙበት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

11156751_10153240544694441_1711534939_n16527_776277319135878_8932629015190402173_n

የዝግጅቱም መርሃ ግብር የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አቢ አማረ እንግዶችን እንኳን ደህና መጣች በማለት በሃገራችን ያለውን አምባገነን ዘረኛ አገዛዝ በህዝባችን ላይ እያደረሰው ያለውን ግፍ ለማስቆም ሁላችንም በአንድ ላይ በመተባበር የሁለገብ ትግሉን በደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በሳኡዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ግፍ አውስተው ለነኚህ ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማስደረግ በይፋ ዝግጅቱን ያስጀመሩ ሲሆን በመቀጠል አቶ ዳዊት የወያኔን የግፍ አገዛዝ አውግዘው እርሳቸውም አገዛዙን ለማስወገድ ያለው ምርጫ ሁላችንም የሁለገብ ትግሉን መደገፍ እንደሚገባን ለህዝቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ቀጣዩ ዝግጅት የነበረው በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የተደረሰውና የግንቦት 7 ህዝባዊ መዝሙር የሆነውን ላንቺ ነው ሀገሬ ላንቺ ነው ላንቺ ነው ኢትዮጵያ ላንቺ ነው የተሰኘውን ዝማሬ ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች የመጡ ወጣቶች በመድረክ ላይ አሰምተዋል። በመቀጠል የግብረኃይሉ ምክትል አስተባባሪ አቶ ደባሱ መለሱ የአርበኞች ግንቦት 7 ጥምረት ውህደትን አስመልክቶ እንዲሁም ያያዙንት የትግል ስልት በተመለከተ ሲያስረዱ ሁሉም ዜጋ በሀገሩ በእኩል የሚተዳደርባት ሀገር እንድትሆን ጥርጊያ መንገዱን እያደረጉልን የሚገኙ በመሆኑ የእኛ ድርሻ የሁለገብ ትግሉን መደገፍ እንዳለብን ጠቁመው የወያኔ ቡድን በሀገራችን ለ24 አመታት ስልጣኑ እንዲራዘም ያደረግነው እኛ ህብረት ባለማድረጋችን እንጂ ወያኔ በርትቶ ወይም ጠንካራ ሆኖ አለመሆኑን ተናግረው በየትኛውም ታሪክ ጥቂቶች ብዙሃኑን ያሸነፉበት ጊዜ አለመኖሩን አስታውቀው የከፋፍለህ ግዛን የወያኔ አገዛዝ በቅርቡ ለመጣል እንደሚቻል አሳውቀዋል።
በተጨማሪም ትግሉ ለምን በኤርትራ በኩል እየተካሄደ እንዳለና በዛ በኩል የሚደረገው ትግል ምን ጥቅም እንዳለው ለታዳሚው በዝርዝር በማስረዳት ኑ ተነሱና በጋራ ደጀንነታችን ሀገራችንን እናድን የሚል ጥሪ አቅርበው ኢትዮጵያ በልጆችዋ ተጋድሎ ወደነበረችነት ትመለሳለች ብለው መልክታቸውን ቋጭተዋል።
ቀጣዩ ተናጋሪ የነበሩትአቶ ዮሃንስ አለሙ  የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅትኖርዌይ ሊቀመንበር ና የግብረሀይሉ ሰብሳቢ ሲሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ ለዜጎቿ ምቹ ያልሆነ መሆኑ ጠቁመው ሁላችንም እራሳችንን መጠየቅ ያለብን እኔ ለሀገሬ ምን ማድረግ አለብኝ ምንስ አድርግያለሁ ብለን ማሰብና ውጠት ጠባቂዎች ብቻ ከመሆን ለውጤት መስራት እንዳለብን አሳስበው እኛ በኖርዌይ የምንኖር ሀገራችንን ነፃ ለማውጣት ተከታታይ ስራዎችን መስራት የምንችል በመሆኑ ለወደፊት ተከታታይ ትግል ማድረግ እንዳለብንና እንዴት መታገል እንደሚቻልም የተወሰኑ የትግል ስልት ነጥቦችን ዘርዝረዋል። እኛም መሰደዳችን አንገብግቦን ሀገር እንዲኖረን መታገል አለብን ብለን መነሳት አለብን ብለው ለአርበኞቻችን የማይነቃነቅ ደጀን እንሁን በማለት ለታዳሚው ጥሪያቸውን አስተላልፈው በሁለገብ ትግል ነፃነታችንን እንጎናፀፋለን ሲሉ ንግግራቸውን ጨርሰዋል።
በመቀጠል የኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም በመጀመሪያ አቋሙን ለታዳሚው ሲገልፅ በዚህ ታላቅ ስብሰባ ላይ የተገኘው እንደኢሳት ጋዜጠኛ ሳይሆን እንደ አንድ ነፃነቱን ናፋቂ  ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ታዳሚው ሀሳቡን የራሱ የፋሲል የግል አስተሳሰብ እንጂ የኢሳት እንዳልሆነ በዚህ መልኩ እንዲረዱት አቋሙን በግልፅ ካስቀመጠ በኋላ የኢትዮጵያ የነፃነት ትግልና በኤርትራ ካለው ግንባር ጋር ስለነበራቸው ቆይታ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥቷል። ከምርጫ 97 ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን የነፃነት ትግል ሲዳስስ የተቃዋሚ ድርጅቶቹን የሚተቹትን በመተቸት የሚደገፉትን በመደገፍ የግል አስተሳሰቡን ሰፋ አድርጎ አቅርቧል። በኤርትራ ውስጥ ስላለው የአርበኞች ግንቦት 7 ወታደራዊ አቅምም ሲናገር በቂና አስተማማኝ ኃይል እንዳለ በአይኑ ያየውን መስክሮ በጣም ቆራጥ የሆኑ ታጋዮች እንደሆኑም በመናገር በፎቶ ግራፍና በቪዲዮ የተደገፉ ማስረጃዎችን አሳይትዋል።
የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ዳሰሳና ትንታኔ ሲያደርጉ ኢትዮጵያዊ ህዝብ በሀገሩ የመኖር ዋስትና በማጣት በተለያየ አለም ተበትኖ ያለው ወገን እየደረሰበት ያለውን ግፍና መከራ ደካማ እኩይ የወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ጫንቃችን ላይ በመሸከማችን መሆኑን በሚገባ ለታዳሚው በማስረዳት የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት አቅም ያለው ሰራዊት መሆኑን አስረድተው በቅርቡም ከደሚት ነፃ አውጪ ጋር በመዋሃድ አብሮ ለመስራት በንግግር ላይ መሆናቸውንና ከሌሎችም ሌሎችም በኤርትራ የሚገኙ ነፃነት ታጋዮች ወደ አንድነት እየመጡ በመሆኑ ከእለርሱ ጋርም በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ወደዚህ ስብሰባ የመጡትም ሰራዊቱ ህይወቱን ሰውቶ ሀገሩን ነፃ ለማውጣት ትግሉን መጀመሩን ጠቁመው እንኳንስ ሀገርን ነፃ የማውጣት ትግል ቀርቶ የየእለት ኑሯችን እንኳን ያለ ገንዘብ ማከናወን እንደማንችል ተናግረው ትግሉን አንድ እርምጃ ወደፊት ለማስኬድ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸውና የህዝቡን ደጀንነት እንደሚፈልጉ ተናግረው ብሄራዊ ውርደትን ለማስቆም በጋራ መስራት እንዳለብን አስረድተዋል።
በመቀጠል በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ወጣቶች ክፍል የተዘጋጀ የብቻ የሆነ ትግል ያደክማል አንድ መሆን ግን ይጠቅማል የሚል ትግል በአንድነት ውጤት እንደሚያመጣና አንድነት ኃይል መሆኑን የሚገልፅ ድራማ የቀረበ ሲሆን አዝናኝና ቀስቃሽ ባህላዊ ሙዚቃ ከውዝዋዜ ጋር እንዲሁም ምግብና መጠጥ ተዘጋጅቶ ነበር።
የውይይት ጊዜም ተዘጋጅቶ ታዳሚዎቹ ለተጋባዝ እንግዶቹ ጥያቄዎቻቸውን እና አስተያየቶቻቸውን በማቅረብ ሰፋ ያለ የውይይት ጊዜ ነበረ። በመጨረሻም የጨረታ ጊዜ በደማቅ ሁኔታና በታላቅ ፉክክር ለጨረታ ቀርቦ የነበረውን የኢትዮጵያ ባንዲራ በከፍተኛ ገንዘብ ለአሸናፊው ተሽጧል። የዲሞክራሲያዊ ለውጥ ድጋፍ ድርጅት ም/ሊ አቶ ዳንኤል የፕሮግራም መዝጊያ ንግግር አድርገው ዝግጅቱ በተያዘለት ሰአት ተጠናቋል።
ይህንን ዝግጅት ከፍተኛ በሆነ ሀገራዊ ስሜትና ቅስቀሳ ከመጀመሪያ ጀምሮ እስከመጨረሻ መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የወጣቶችና የሴቶች ክፍል ኃላፊ ወ/ሪት የሺሃረግ በቀለ እና የወጣቶች ክፍል አመራር አቶ ይበልጣልጋሹነበሩ።
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ