Tuesday, 10 February 2015

አቶ አርከበ እቁባይ መለስ ዜናዊን መግደል ጀምረዋል (ሪፖርታዥ)



አቶ አዲሱ በኢህአዴግ ድርጅታዊ መዋቅር ውስጥ እንጂ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ የሉም። አቶ አርከበ ደግሞ በመንግሥት እንጂ በድርጅቱ መዋቅር ውስጥ የሉም። መዋቅር የማያገናኛውቸው ከሆነ ሁለቱን ከአንድ ስብሰባ ምን አስቀመጣቸው? የመከራከሪያቸው ፍሬ ነገርስ ስለምን የመለስ አስተምህሮ ሆነ? የመለስ አስተምህሮ ራዕይና ሌጋሲ የአገሪቱ አቅጣጫ መመሪያ ማስፈራሪያ እየሆነ ዋነኞቹን ባለሥልጣናት ሳይቀር እያከራከረ ይመስላል። ወደታች ወረድ ብለን እንመለከተዋለን።

Arkebe Equbay - Ethiopia

በአንድ የቅርብ ስብሰባ ላይ አቶ አዲሱ ለገሠ አቶ አርከበን ሲነቅፉ “ ቆይ ቆይ አርከበ እኔ እዚህችጋር አንድ ጥያቄ አለችኝ። እስኪ ይሄ ያዘጋጀኸው ዶክመንት ከመለስ አስተምህሮ ጋር እንዴት እንደሚሄድ አስረዳኝ……”


ለማናኛውም አቶ መለስ ዜናዊ ሞልተውን ለሄዱት የውድቀትም ሆነ የእድገት ሰሌዳ፣ ከአንዳቸው እንደርስ ዘንድ ምን ያህል ጊዜ ይቀረናል? በራዕይ የተገለጠላቸውን የኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ምልክቱን እናይ ዘንድ ምን ያህል መጓዝ ይኖርብናል? ወይስ ደርሰናል ? ወይስ አቅጣጫውን ስተን ሌላ መንገድ ይዘናል? ከእድገቱ ወይስ ከቁልቁልቱ አፋፍ ላይ ነን? በፈጣኑ እድገታችን ፋፍተን እንደ ጽጌረዳ ፈንድተን እንፈካለን ወይስ እንደ ፈንጂው እንጠፋለን? ወዴት እየሄድን ነው?

በወቅቱ እንደተዘገበው 8ኛው የኢህ አዴግ ጉባዔ የተካሄደው ከመስከረም 5-7/2003 ዓ.ም አዳማ የኦሮምያ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነበር። ጉባዔውን በመምራት ላይ የነበሩት አቶ መለስ፣ የአምስት- ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ የተደረገው ውይይት በቂ እንደሆነ ገልፀው፣ ‹‹የቀረበውን ሪፖርት መፅደቁን የምትደግፉ፣ ያደረጋችሁትን ባጅ ከፍ አድርጋችሁ አሳዩ›› ሲሉ ጠየቁ። ጉባዔተኛው በሙሉ አንገታቸው ላይ ያንጠለጠሉትን ሰማያዊ የጉባዔ ተሳታፊነት መለያ ወደ ሰማይ ቀሰሩ።
‹‹እቅዱን የምትቃወሙና ድምፅ የማትሰጡ?››
ማንም የለም።
“የአምስት- ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ጸድቋል።” አሉ።
አዳራሹ በጭብጨባ ተሞላ።
የአቶ መለስ በዚህ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር እንዲህ አሉ

IMG_0683

አቶ መለስ ዜናዊ ከሞቱ በኋላ ግን ድርጅታቸው ዛሬ ላይ ቆሞ ሲያየው የአቶ መለስ እቅድ ያለቅጥ የተለጠጠ ነበር። ምክንያቱም አልተሳካም። የማይሳካው ነገርም የታቀደው ሆን ተብሎ ነው። አቶ መለስን ልክ አልነበሩም በማለትና እሳቸውን በማምለክ መካከል በመንገላታት ላይ የሚገኘው ድርጅታቸው በጣም የሚያስቅ መግለጫ ይዞ ወጥቷል። የአቶ መለስን ስህተት እንኳ እንድ ራዕይ አይቶት ከሰማይ ከዋክብትን ከማርገፍ ጋር አመሳስሎታል። በሌላ በኩል ደግሞ አቶ መለስ ከላይ በንግግራቸው “wdnþ× lþb‰L ygbà xK‰¶nT ymSfN«„N xdU tÌqÜmN” እ ያሉትን አደጋ ዛሬ መልሶ የሚያመጣ ወይም ድላቸውን የሚቀለብስ አደጋ በገዛ ጓዶቻቸው መጥቶባቸዋል። በቦንድ ሽያጩ ትላልቅ ኢንደስትሪ ዞኖችን በማቋቋም ስም ትላልቅ የውጭ ኢንቨስተሮችን ጓዶቻቸው ወደ አገር ውስጥ እየጋበዙላቸው ነው። ምክንያቱም አቶ መለስ ያሉት እድገት አልመጣም። አገሪቷ በኢኮኖሚ ቀውስ ተዘፍቃ ከሌሎች ችግሮቿ ጋር አብጣ ልትፈነዳ ሰከንድ የምትቆጥር መስላለች…. በኢህአዲግ አመራሮች መካከል ይቅር እንጂ አቶ መለስም ድርጅታቸውንና አገሪቱን ከማይሆን ነገር ውስጥ ዘፍቀዋት ሄደዋል….

መወቃቀስ መያዛቸው ይሰማል። ቀጣዩ አቅጣጫ ይህ ሊሆን ይገባል አይገባም መባባላቸው እየተሰማ ነው። ክርክሩ ንትርክ ከንትርክም አልፎ የተካረረ መስመር እየያዘ መምጣቱ ይሰማል። ይህ ወደ ፖለቲካው ሽኩቻ አድጎ ወይም ሰበብ ሆኖ እንደ ኤርትራው ጦርነት ክፍፍል ዘመን ኢህአዴጎችን ለሁለት እንዳይከፍላቸው አስግቷል። ወይም አስጎምዥቷል።
በሌላ አነጋገር አቶ መለስ ልክ ነበሩ ወይስ አልነበሩም ይከለሱ ወይስ አይከለሱ የሚል ትርጓሜ እየፈጠረ ይመስላል። የመለስ ራዕይ ወይም አስተምህሮ አራማጆችና አስጠባቂዎች ባንድ በኩል ከላሾችና ምንትስሊብራሎችየተባሉትደግሞ በሌላ በኩል ሆነው ለመወጋገዝ በተጠንቀቅ ሆነዋል። የክፍፍል ዓይነቱ ብዙ ነው። ፓርቲ ውስጥ ያሉትን የመንግሥት ሰዎች በአንድ በኩል መንግሥት ውስጥ የሌሉ የፓርቲ ሰዎችን ደግሞ በሌላ በኩል ማሰለፉም እየተሰማ ነው። ለዚህ ሁሉ የልማትና የትንራንስፎርሜሽን እቅዱ ዋነኛው መነጋገሪያ ወይም የመዋጊያ ሜዳ መስሏል።

ሰበብ ሆኖ የሚያነጋግረው ይሄ የ 5 ዓመት እቅዱ ዋነኛው ይሁን እንጂ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ እያደገ የመጣው መናናቅና ዓይን የሚሞላ ሰው በድርጅቱ አመራር ውስጥ አለመገኘት መሆኑም ይወራል። ሥልጣን የባለ ራዕዮች ስለሆነ የነበረውን ማስቀጠል ወይም አዲስ ራዕይ መውለድ ወቅቱ የጠየቀው ጥያቄ መስሏል። ይህ ሁሉ ተደማምሮ የመጀመሪያውን እቅድ አፈጻጸምን በመገምገምና በሁለተኛው ትራንስፎርሜሽን አስተቃቀድ ላይ አለመግባባት ደንቅሯል። በዚህ ጽሑፍ የምናየው እነዚህን ይሆናል።

የገዢው ፓርቲ የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በየዓመቱ የአገሪቱን አጠቃላይ የፖለቲካና ኢኮኖሚ አቅጣጫና ግብ አስመልክቶ ግምገማ ያደርጋሉ። በተለይ የአምስት ዓመቱን የልማትና የትራንስፎርሜሽን አፈጻጸም ይቃኛሉ። አሁን የአምስት ዓመቱ እቅድ ሰኔ ላይ አልቆ ሁለተኛው የአምስት ዓመት የልማትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ይፋ መደረግ ይጀምራል። በዚህም መሠረት ከወራት በፊት በጥቅምት 2007/ ኖቨምበር 2014 ላይ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በዚሁ ስብሰባ የመጀመሪያውን እቅድ ጉድለቶችና ችግሮች ገምግሞ በሁለተኛው የአምስት አመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መነሻ ማዕቀፍ ላይ ተወያይቶ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ እንዲመጣ አዟል፡፡ የእቅዱ ዋናው ማጠንጠኛ አቅጣጫ የኢንዱስትሪያላዜሽን ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥ እንደሚሆን አስምሮበታል፡፡

ይሄ የኢንደስትሪያላዜሽን ትራንስፎርሜሽን ወይም የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ጉዳይ “ዋነኛ” ሆኖ መውጣቱ በአቶ መለስ ብዙም የማይደገፍ አካሄድ መሆኑና አፈጻጸሙም ላይ ልዩነት መኖሩ ይታወቃል። የትራንስፎርሜሽኑ ምሶሶ ኢንደስትሪ መሆኑ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት ቢኖረውም በኢንደስትሪ ዞን አመሠራረት ፖሊሲ ዙሪያ አሁን ያለው የኢህአዴግ አመራር ለሁለት ተከፍሏል። የኢንዱስትሪ ዞኖቹ የት የት አካባቢ ነው መቋቋም ያለባቸው መጠናቸውና አገልግሎታቸው እንዴት ይሆናል የፋይናንስ ድጋፉንስ ከየት ያገኛሉ በየትኞቹ የምርት ዓይነቶች ላይ ማተኮር አለባቸው እነዚህ ሁሉ ኢህአዴጎቹን ያስማሙ አልሆኑም።

ለምሳሌ አንዳንዶቹ ኢንደስትሪያል ዞን (ፓርክ) ላይ ማተኮር አለብን ባዮች ናቸው። የሆነ አካባቢ ትልቅ ቦታ ተከልሎ የተንጣለለ መሬት ይሰጣል። ገንዘብ ይቀርባል። ባንኩ ታክሱ ሁሉ ነገር እዚያው ይጠናቀቃል። ልክ ሞጆ ላይ ለቻይኖቹ እንደሆነው ትልቅ ኢንደስትሪ ዞን ማለት ነው። እዚህኛው ላይ ጥያቄ የሚያነሱት አመራሮች እንደዚያ ያለ ትልቅ ዞን ሲቋቋም የአገር ባለሀብቶች አቅሙ አይኖራቸውም። እንደዚያ ያለ ካፒታል የሚኖራቸው የውጭ ኩባንያዎች ስለሆኑ አገር ቤት ያለው ባለሀብት እየቀነሰ ይመጣል። ያ ደግሞ እንደ ኬንያና መሰል አገሮች ኢንቨስትመንቱን የሚቆጣጠሩት የውጭ ኢንቨስተሮች ይሆናሉ። ይህ አገሪቱን አሳልፎ ለውጭ ባለሀብቶች የመክፈት ስለሆነ የኒዮ ሊብራሎች አስተሳሰብ ነው። ይህ ከኢህአዴግ መርህ፣ ከመለስ አስተምህሮ ጋር ይቃረናል። ስለዚህ እናንተ ካላሾች በራዦች (ሪቪዥኒስት) ናችሁ…. ባዮች ናቸው።

ከሱ ይልቅ በትንናሽ መንደሮች (ሳተላይት) መካከለኛ ኢንደስትሪ ማቋቋም እንደሚሻል ይከራከራሉ። በየተወሰነው ትናንሽ ከተማ ትናንሽ የጎጆ ኢንደስትሪዎችን ብንቋቁም ይሻላል። ያቺ ለአካባቢው ነዋሪ የሥራ እድል ትፈጥራለች። አካባቢውም ለኢንደስትሪው የሚሆን ግብአት (ጥሬ እቃና የሰው ኃይል) በመስጠት ይደግፋል። ስለዚህ መደጋገፍ ይኖራል፡ ፡ ለትንንሽ መንደሮችና ከተሞች እንዲሁም ለገበሬዎች ትንሽ ትንሽ እየሰጡ ከተሠራ እነሱ እያደጉ ይመጡና በረጅም ጊዜ ሂደት ውስጥ ራሳቸውን ወደ ትላልቅ ኢንደስትሪዎች ማሳደግ ይችላሉ ባዮች ናቸው።

ትራንስፎርሜሽን አብይ ዓላማው ገጠሬን ወደ ከተማ መለወጥ ግብርናን ወደ ኢንደስትሪ መቀየር ኤክስፖርት ላይ የተመሠረተ ምርት በማፍራት የአገሪቱን ገቢና የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል የሚለው ሲናገሩት ቢጣፍጥም አብረው ሊሄዱ የሚችሉ የአመራርና የአስተዳደር ብቃት በቦታው አልተገኘም። የግል ባለሀብቱም ሚናው በግልጽ አልተመለከተም። አንደኛ ይህንን ህልም ሊደግፍ የሚችለው የግል ባለሀብቱ የፋይናንስ ድጋፍ ሊያገኝ የሚችልበት የብድርም ሆነ የፋይናንስ ምንጭ የለም። የአገር ውስጥ ባንኮች እንዳይበድሩ በመመሪያ ታስረዋል። እያንዳንዱ ባንክ የሚያበድረውን ብድር 27% ቦንድ እንዲገዛ ይገደዳል። ይህ ማለት ለግል ባለሀብቱ ሊያበድር ከሚችለው ገንዘብ ለቦንዱ ይከፍላል ማለት ነው። ስለዚህ ባንኮች ብዙ ባበደሩ ቁጥር ክፍያቸው እየመጨረ ይሄዳል፡፡ በመካከሉ ባለሀብቱ ገንዘብ አያገኝም። ለዚሁ ተብለው የተቋቋሙት እንደ ልማት ባንክ ያሉት የመንግሥት አበዳሪዎችም ቢሆኑ የባንኩ ኃላፊ ሰሞኑን እንደገለጹት ከሆነ መስፈርቱ ቀላል አይደለም። ለተመረጡ ዘርፎች ያውም ተበዳሪዎች ቢያንስ 30 ከመቶ የማዋጣት ኃላፊነት ይኖርባቸዋል። ከውጭ ባለሀብቶች ይልቅ የአገር ውስጥ ባለሀብቶች ጋር ሲስተያይ የአገር ውስጥ ባለሀብቶች ከባንኩ ብድር የማግኘት ተጠቃሚነታቸው ከመቶ ፐርሰንት ወደ 75 በመቶ እየወረደ መምጣቱም ተገልጿል። ይህም እያደገ ሄዶ ወደፊት አብዛኛውን የባንኩን ብድር የውጭ ባለሀብቶች ጠቅልለው ሊወስዱ የሚችሉበት አቅጣጫ ይታያል።
ሌሎቹ ደግሞ ሲከራከሩ የፋይናንስ ምንጫችንን ከውጭ ቢሆን አፈላልገን እናገኛለን። ለዚህም መፍትሔ የተለያዩ የፋይናንስ ምንጮችን አፈላልጎ ማግኘት ነው እንጂ እንዲሁ በር ዘግቶ መቀመጥ አያዋጣንም ባዮች ናቸው። የቦንድ ሽያጩ ነገር የመጣው እዚህጋ ይመስላል።።
meles zenawi

መለስ ቢኖሩ ቦንዱ አይኖርም! መለስ እየሞቱ ነው!


የመለስ ሌጋሲ አስጠባቂዎቹ አመራሮች እነ አቶ በረከት እና አባይ ፀሐዬ ቦንዱን በጥብቅ ተቃውመውታል። የቦንዱ ሽያጭ የፓርቲው ዶክመንት ከሚፈቅደው ውጭ አገሪቱን ለውጭ ኃይሎች በርግዶ መስጠት ነው። ለትላልቅ ፕሮጀክቶቻችን የአገር ውስጥ የፋይናንስ አማራጮችን ገና ተጠቅመንና ፈልገን አልጨረስንም። በኒዮ ሊብራሎች ኃይልና ግፊት ነው እዚህ ውስጥ የገባነው ብለው ያምናሉ። ቦንዱ ከኢህአዴግ እምነት ውጭ የተደረገ ፣ ሁሉንም ነገር ከፍቶ የመስጠት ኢኮኖሚውን ለውጭ ኃይላት የመክፈት የመጀመሪያው ዝንባሌና ምዕራፍ ነው። ነገ መለስ ተሟግቶ ያቆየውን ቴሌ ይሸጥ፣ ባንኮች ለውጭ ባለሀብቶች ባለቤትነት ክፍት ይሆኑ…የሚለው ክርክር ጅማሬ ነው ባዮች ናቸው።

የእነዚህ ከፍተኛ አመራሮች ምሬት ስናይ ምናልባትም ወደፊት “ቦንድና ሉአላዊነት በኢትዮጵያ” የሚል መጽሐፍ በክፍፍል አፈንግጦ በሚወጣ ሌላ ባለሥልጣን እናነብ ይሆናል። ምክንያቱም ጨዋታውና መወነጃጀሉ ሁሉ እንደ ኢትዮ ኤርትራ ወቅት ክፍፍል ከላሽና ተቸካይ መባባልን እያመጣ ነው። ሌሎች ተንበርካኪ ይሏቸው የነበሩ ባለሥልጣናት አሁን ደግሞ በተራቸው ተንበርካኪ የሚባሉበት ሁኔታ የተፈጠረ ይመስላል።

የክፍፍሉን ደረጃ አስገራሚ የሚያደርገው ሌላው ነገር ደግሞ የቦንዱ ሽያጭ ውሳኔ የተወሰነበትና ለህዝብ ይፋ የተደረገበት መንገድ ነው። ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃ/ማርያም (ከአማካሪያቸው አቶ አርከበ ጋር) ቦንድ ሽያጭ የመግባቱን ውሳኔ ሲወስኑ የኢህአዴግን ሥራ አስፈጻሚ አልተነጋገረበትም። በመጀመሪያ በሚኒስትሮች ም/ቤት ተወሰነ። ከዚያ ወደ ፓርላማ ሄደ። ከፓርላማውም በፓርላማው ጠቅላላ (በአዳራሹ) ሳይሆን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ብቻ ነው የታየው።

ይህን የሰሙት የፓርቲው የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባላት ተቆጡ። እነ ኃ/ማርያም ሥራ አስፈጻሚውን ሳታስፈቅዱ ለምን ገባችሁበት ተብለው ሲጠየቁ ፍርጥም ያለ ምላሽ ሰጡ። 1ኛ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሊነጋገር የሚገባበት ጉዳይ አይደለም። ሁለተኛ የመንግሥት ሚኒስትሮችና ፓርላማው ተነጋግሮበት ወስኗል። 3ኛ በዚያ ላይ የሚኒስትር ም/ቤት አባላትም ውስጥ ቢሆን የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባላት አሉ። ሁሉም የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚዎች የሚኒስትሮች ም/ቤት አባል ባይሆኑም ከሞላ ጎደል ሁሉም ሚኒስትሮች ግን የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባላት ናቸው። የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባላት 60 ሲሆኑ የሚንስትሮች ም/ቤት አባላት ደግሞ 30 ናቸው። እዚህ ላይ አቶ ኃ/ማርያም ሥር የተጠለሉ የፓርቲው አንጃዎች (ከአቶ መለስ የተማሩትን) ጨዋታውን በሚገባ አውቀውታል። እንዲያውም ይባስ ብለው እንዴ ምን ማለት ነው? ምንስ ቢሆን እኛን እንዴት አታምኑንም? እዚያ ቦታ ስታስቀምጡን ከድርጅታችን ውጭ እንዴት ልንወስን እንችላለን በማለት ተቆጡ።

ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆነና እነዚያም እንዲሁ ይተዋወቃሉና ውስጣቸው እያረረ በሉ ላሁኑ ይሁን አሉ። እንደዚህ ዓይነት ነገር ግን ለወደፊቱ መደገም የለበትም ይህ ቀላል ውሳኔ አይደለም የድርጅቱን መርሆ የታላቁ መሪያችንን አስተምህሮ የሚቃቀረን ነው አባሎቻችንን ማረጋጋት ይኖርብናል ዓይነት ነገር ብለው ሂስ አስውጠው እንዳይደገም ማስጠንቃቂያ ሰጡ።

ለዚህም ይመስላል አቶ ሱፍያን ወዲያው አደባባይ ወጡና ስለቦንዱ ስለሶቭሪን ቦንዱ መግለጫ ሰጡ። “ሶቭሪን ቦንድ መሸጥ ማለት የኢኮኖሚ ፖሊሲያችንን ቀይረናል ማለት አይደለም። ለሚቀጥለው ሶስትና አራት ዓመት ሌላ የቦንድ ሽያጭ አናወጣም” ብለው ተናገሩ። እዚህ ላይ ፖሊሲ ስለመቀየር አለመቀየር መናገርን ምን አመጣው? ቦንዱንስ የማይሸጡት ለምንድነው? ያቀርብነው ቦንድ የ1 ቢሊዮን ቢሆንም ያገኘነው ግን 2.5 ቢሊዮን ለመግዛት ፈቃደኛ የሆነ ገበያ ነው። ያህን ያህል ገበያ ካገኙ፣ ቦንዱም ያን ያህል ተፈላጊ ከሆነ፣ ለሚቀጥሉት ዓመታት አንሸጥም ማለትን ምን አመጣው? አይለመደንም እንደማለት ይመስላል።
ይህ ዓይነት ልዩነትና መቀበጣጠር የኖረው ሁሉም መሪያችን ነው ብለው የሚያከበሩት ሰው ባለመኖሩ ነው። ሁሉም የሚያከበሩት መሪ (ግለሰብና) ድርጅት የሌለበት ሁኔታ ነው የሚታየው። አንዱ ላንዱ ያለው አክብሮት ጤነኛ አይመስልም። መጥፎ ስሜትም እያሳደሩ ነው። ይህ ከኢኮኖሚ ወጥቶ የፖለቲካ ጉዳይ የማይሆንበት ምክንያት የለም። እነዚህ ሰዎች ልዩነታቸውን ምን ያህል በሰለጠነ መንገድ ይፈታሉ? ከዚህ ገፍተው የሞትና የሽረት ትንቅንቅ (የሰርቫይቫል) ቢያደርጉና ቢሞክሩ ሁሉም ነገር ሌላ መልክ ይኖረዋል።

እነ አርከበ/ኃይለማይርም የቦንዱን ውሳኔ ለብቻቸው ሲወስኑ ምክንያት ነበራቸው። ለምሳሌ ከአቶ መለስ ራዕይ የተለየው የኢንደስትሪያል ዞኑ ፖሊሲ ጉዳይ ሁለቴ ተጥሏል። ቦንዱን በራሳቸው ከወሰኑ በኋላ ለፓርቲው ማስረዳት የመረጡት በዚህ ምክንያት ነው። ይህንም ብናቀርብ ይጥሉብናል። ሰለዚህ ለራሳችን ለምን አናደርገውም የሚል ብልጠት መኖሩ ተነግሯል። በሌላ በኩል ከአቶ መለስ ራዕይ ጋር በተቸከሉትና በቻልነው ፍጥነት ተጠዳድፈን ካፈጠጠብን ቀውስ እውንጣ በሚሉት አባላት መካከል ፍትጊያ ቢርኖም ችግሩ በአንድና በሁለት የመከፈል ሳይሆን ቢያንስ ወደ ሶስት የሚጠጋ ቡድን መፈጠሩም ይሰማል።

በረከት አዲሱ አባይ ፀሐዬ የመለስ ሌጋሲ እናስጠብቅ ባዮች ሆነው አንድ ቡድን ናቸው። አርከበ ዋነኛው ሆኖ ኃይለማርያም ሱፍያን ተክለወልድና ደብረፅዮን ደግሞ ሌላኛው ቡድን ሲሆኑ የማሻሻያ ለውጥ ያስፈልጋል ባዮች ናቸው። ጄኔራል የተባሉት እነ ሳሞራ የመለስ ራዕይ ከሚለው ውጭ ጉዳዩ ብዙም ስለማይገባቸው አገሪቱን በሥልጣን እያሳደረ ነው የሚባለው ሠራዊታቸው ከማንኛቸው ጋር እንደሚቆም ለመገመት ሳያዳግት አልቀረም። ገና እጅ ያልሰጡት እነወይዘሮ አዜብና ቀሪዎቹ የህወሓት ሥራ አስፈጻሚዎች ከሠራዊቱ ጋር ማንዣበባቸው ይሰማል።

ይህ ጽሑፍ በዘኢትትዮጵያ ጋዜጣ ላይ ታትሞ ወጥቷል; ርዕሱን ግን እኛ ቀይረነዋል::



Monday, 9 February 2015

Ethiopia’s stifled press

 February 9 at 3:08 PM
WHILE ENJOYING its status as an international development darling, Ethiopia has been chipping away at its citizens’ freedom of expression. The country now holds the shameful distinction of having the second-most journalists in exile in the world, after Iran. That combination of Western subsidies and political persecution should not be sustainable.
According to a new report by Human Rights Watch, at least 60 journalists have fled the country since 2010, including 30 last year, and at least 19 have been imprisoned. Twenty-two faced criminal charges in 2014. The government closed five magazines and a newspaper within the past year, leaving Ethiopia with no independent private media outlets. With the country headed toward elections in May, the pressure on the media has undermined the prospect of a free and fair vote.
Ethiopia has long been known for its censorship and repression of the media, but the situation has deteriorated in recent years. According to theCommittee to Protect Journalists, the country has since 2009 “banned or suspended at least one critical independent publication per year.” After the death of prime minister Meles Zenawi in 2012, successor Hailemariam Desalegn has tightened the regime’s stranglehold on the press. Even Ethiopia’s rival Eritrea looks better: It released several imprisoned journalists last month.
As Human Rights Watch documents, journalists and media outlets who dare publish critical articles routinely receive threatening phone calls, texts and e-mails from party officials and security personnel. Journalists’ movements are often restricted outside of the capital, Addis Ababa. Sources who talk to foreign journalists and human rights organizations can face threats and detainment.
The repression extends across the media ecosystem. State agents harass printers and disrupt distribution processes associated with critical publications. Journalists who flee into neighboring countries are tracked and threatened. The government blocks Web sites from the Ethiopian diaspora, and it has jammed signals of foreign broadcasters, including Voice of America.
Much of the persecution has come under the guise of counterterrorism by a regime that has been a player in the fight against the al-Qaeda-allied al-Shabab. At least 38 journalists have been charged under a 2009 “anti-terrorism proclamation” and the criminal code. In 2012, prominent journalist and blogger Eskinder Nega was jailed for 18 years on charges of terrorism after criticizing the government’s repression.
Despite these policies, Ethiopia has retained its status as a U.S. ally and recipient of large amounts of U.S. development assistance — including $373 million for health and humanitarian programs in 2014. By contrast, U.S. spending on democracy and human rights assistance in Ethiopia has fallen dramatically in the past several years, from $3.4 million in 2012 to $162,900 in 2014. The decline in assistance for human rights bows to a 2009 law that prohibits nongovernmental organizations receiving more than 10 percent of their funding from abroad from conducting human rights advocacy.
The State Department recently spoke out against the media crackdown. But more than words should be at stake. The Obama administration should link continued aid to the release of imprisoned journalists and bloggers, and it should enlist other Western aid donors to do the same. The West should not be subsidizing a regime that is one of the world’s leading persecutors of journalists.
Correction: An earlier version of this editorial incorrectly reported that Ethiopia’s government closed five newspapers and one magazine within the past year. The government shut five magazines and one newspaper in 2014, according to Human Rights Watch. The following version has been updated.

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ደብዳቤ



ቀን 02/06/2007 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- የልጄ ተመስገን ደሳለኝን ጉብኝት ይመለከታል

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከአብራኬ የወጣ ሁለተኛ ልጄ ነው፡፡ ገና ከህፃንነቱ ጀምሮ ለሰው አሣቢ፣ ሀገር ወዳድና ታታሪ ስለመሆኑ ከእኔ በላይ የሚያውቁት ይመሰክራሉ፡፡ ልጄ ተመስገን ለወገኔ አሰብኩ ባለ በእስር ቤት ያለጎብኚ እየተሰቃየብኝ ይገኛል፡፡ መቼም፣ የእናት ሆድ አያስችልምና እባካችሁ ልጄን ታደጉት፡፡ እባካችሁ ቢያንስ ካለበት እየሄድኩ የልጄን አይን እንዳይ እንዲፈቀድልኝ ተባበሩኝ፡፡ የልጄን ድምጽ ከሠማሁ ይኸዉ አንድ ወር ሞላኝ፡፡ ታናሽ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ለወንድሙ ብሎ የቋጠረዉን ምሣ ይዞ ዝዋይ ማረሚያ ቤት ቢሄድም በማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎች ተደብድቦ የያዘውን ምግብ እንኳ ሣያደርስ ሜዳ ላይ ተደፍቶ ተመልሷል፡፡ መቼም እናንተም ልጆች ይኖራችኋል፤ ደግሞም የልጅን ነገር ታውቁታላችሁ፡፡ እኔ አሁን በእርጅና ዕድሜዬ ላይ እገኛለሁ፡፡ ከአሁን በኋላ ብቆይም ለትንሽ ጊዜያት ነው፡፡ በዚህች ጊዜ ውስጥ ልጄን እየተመላለስኩ እየጠየኩ፣ ድምፁን እያሰማሁ፣ አይዞህ እያልኩ ብኖር ለእኔ መታደል ነበር፡፡ እባካችሁ እርዱኝ የልጄ ድምጽ ናፈቀኝ፡፡ እሱን መጎብኘት የተከለከለበት ምክንያት ምን እንደሆነ እንኳን እስካሁን አላወቅሁም፡፡ ከወንድሙ ድብደባ በኋላም ጥር 10 ወደ ጠዋት አካባቢ የሄዱት ጓደኞቹ እና ወንድሞቹ ሳያዩት ተመልሰዋል፡፡


ተምዬ ስታመም የሚያስታምመኝ፣ “አይዞሽ እማዬ” የሚለኝ ረዳቴ ነው፡፡ ሌላ ዘመድ የለኝም፡፡ የምተዳደረውም ልጆቼ ለፍተውና ደክመው በሚያመጧት ትንሽ ብር ነው፡፡ ዛሬ ግን ይኸዉ ልጆቼም ወንድማቸውን ለማየት እየተንከራተቱ ነው፡፡

በእናታችሁ ይዣችኋለሁ፤ ከቻላችሁ ልጄ እንዲፈታልኝ እና እኔም ያለችኝን ቀሪ የእድሜ ዘመን አይን አይኑን እያየሁ እንድኖር እንድታደርጉልኝ፤ ይህን ማድረግ ከአቅም በላይ ከሆነ ደግሞ ካለበት ድረስ እየተመላለስኩ እኔና ሌሎች ልጆቼ እንዲሁም ወገኖቹ እንዲጠይቁት ቢደረግልኝ ስል በአክብሮት እጠይቃችኋለሁ፡፡ ልጄን አውቀዋለሁ፡፡ አንድ ነገር ሲገጥመዉ ሆድ ይብሰዋል፡፡ ቢያንስ እንኳን ቤተሰቦቹን ሲያይ ስለሚፅናና ይኸዉ እንዲፈቀድልኝ እማፀናለሁ፡፡ እኔ ምንም አቅም የሌለኝ አሮጊት ነኝ፡፡ ሁሉንም ለናንተ ሠጥቻችኋለሁ፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር እንደምታስተካክሉልኝ እና እንደገና የልጄን ፊት እንዳይ እንደምታደርጉኝ ሙሉ ተስፋ አለኝ፡፡

እንግዲህ የየካዉ ቅዱስ ሚካኤል ይከተላችሁ፡፡ መቼም የእናትን ሆድ ታውቁታላችሁ፤ የልጅ ነገር አያስችልም፡፡ ሆድም ቶሎ ይሸበራል፡፡ ስለዚህ እባካችሁ እኔንም ልጆቼንም እርዱን እንላለን፡፡

ግልባጭ
- ለጠ/ሚኒስተር ፅ/ቤት
- የህግና፣ ፍትህና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
- ለአፈ-ጉባኤ ፅ/ቤት
- የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ)
- ለእምባ ጠባቂ
- ለአሜሪካ ኢምባሲ
- ለእንግሊዝ ኢምባሲ

ከሰላምታ ጋር

ወ/ሮ ፋናዬ እርዳቸው
_________________________________________________________________________
_________________________________________________

ለጋዘጠኛ ተመስገን ደስአለኝ  አጋርንቶን  በማሳየት በፌስ ቡክ ባለው ገፅና ለሚማለከተው ክፍል ደብዳቤ በማስገባትና  በቻሉት መንገድ ሁሉ ትብብሮትን   ይግለፁ ᎓᎓ የህግ የበላይነት በኢትዮጵያ እንዲከበር የሁላችንም ተሳትፎ ወሳኝ ነው ᎓᎓


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የመናገር ነጻነቱን በመጠቀሙ ብቻ፣ የሶስት አመት እስራት ተፈርዶበት ቤተሰቦቹ ካሉበት 162 ኪሎ ሜትር ርቆ በዝዋይ እስርቤት ከተከረቸመበት እነሆ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ ላለፉት 30 ቀናት ደግሞ በህገ መንግስቱ አንቀጽ ሃያ አንድ የተሰጠው መብት ተጥሶ፤ በቤተሰብም ሆነ በወዳጅ ዘመዶቹ እንዳይጠየቅ ተከልክሏል፤ የምግብና የህክምና አገልግሎትም አያገኝም፡፡
ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት በበይነ-መረብ ዘመቻ ቢያንስ ይህንን የማረሚያ ቤቱን እርምጃ እንቃወማለን፤ ሲቀጥልም ጋዜጠኝነት ወንጀል አለመሆኑን እንሰብካለን፡፡ ተመስገን በቤተሰብና በወዳጅ ዘመዶቹ እንዲጠየቅ፣ ምግብ እንዲገባለትና የህክምና አገልግሎት የማግኘት መብቱ እንዲከበር አበክረን ድምጻችንን እናሰማለን፡፡ ተመስገን የታሰረለትን ዓላማና እየከፈለ ያለውን ዋጋ እንዘክራለን!
https://www.facebook.com/pages/Free-Temesgen-Desalegn/147763648696884


ጓዶች ሆይ፦ ምርጫውን እርሱት! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ -ዝዋይ እስር ቤት )


(መልዕክት-አብዬታዊያን)
ተመስገን ደሳለኝ
ከዝዋይ እስር ቤት

“ባለወር ተተካ
ተቀበለኝ ትግሌን እንካ”
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)

…ሲያሻው እየጋመ፤ ሲያሻው እንደበረዶ እየቀዘቀዘ በመካሄድ ላይ ያለው የፀረ-ጭቆና ትግል እንደዋዛ ግማሽ ክፍለ ዘመን አስቆጠረ፡፡ የሂደቱ ክፉ ጎን ደግሞ የአያሌ ብርቱ ወንድም-እህቶቻችንን የህይወት ግብር እየጠየቀ ዛሬ ድረስ ተጉዟል፡፡ በተለይም ሁለቱ ቀደምት አብዮቶች (የ1966ቱ እና የ1983ቱ) ብረት-ነከስ ናቸውና የትውልድ ክፍተት እስከመፍጠር የደረሰ ዕልቂት ስለመሸከማቸው በደም የተፃፉት ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ ከመዓቱ የተረፉት የዓይን እማኞችም ለወቅቱ መከራ ምስክሮች ናቸው፡፡ እነዚህ አብዮቶች፣ አነሰም በዛም፣ የየራሳቸውን በጎ አበርክቶ ትተውልን ማለፋቸው ባይካድም፤ የተከፈለው መራራ ዋጋ ግን ለውጤታቸው በዝቶባቸዋል፡፡ ህይወት የተማገደላቸው እኒህ የለውጥ ንቅናቄዎች፣ የተነሱለትን ምክኒያት የዘነጉ ዋጋ-ቢስ አገዛዞችን በማዋለድ ተጠናቀዋል፡፡ እኔና የትውልድ ተጋሪዎቼም ቀሪውን የለውጥ ጥያቄ በድል ለማጀብ የቀለም አብዮትን ወደ መምረጡ ጠርዝ የመጣንበት መግፍኤ ይኅው ነው ብዬ አምናለሁ፡፡
የ1983ቱ የኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም ውድቀትን ተከትሎ የስልጣን ባለቤት የሆኑት የማሌሊት ጓዶች ናቸው፡፡ ተረኞቹ ባነበሩት ሥርዓት የዲሞክራሲና የሰብአዊ መብቶች ልዕልናን በህገ-መንግስት ሳይቀር መደንገጋቸው የሚስተባበል ባይሆንም፤ ይህንኑ መብት ለመጠቀም በሞከሩ የተቃውሞ ስብስቦች ላይ የወሰዱት ተከታታይ የኃይል ጭፍለቃዎች ግን የ“አዋጁን በጆሮ”ነት ይመሰክራሉ፡፡ በዚህ መሰሉ ግብ-ግብም ህልቆ-መሳፍርት የአገሬ ልጆች የህይወት መስዋዕትነት መክፈላቸውን፤ እስር ቤቶችን ማጨናነቃቸውንና በስደት መላውን ዓለም ማዳረሳቸውን አንዘነጋውም፡፡ በርግጥም ይህን መዘንጋት ለደመ-ቀዛቃዛ ገዢዎቻችን ተጨማሪ ድል ነውና መቼም ቢሆን አናደርገውም፡፡
ሥርዓቱ በየዕለቱ የሚፈጥረውን መሰል ሰቆቃዎች አስተውለው በዝምታ ሊያልፉ ያልቻሉት፤ የወደቁትን እየተራመዱ፤ የደከሙትን እየተኩ፤ “ፋኖ-ተሰማራ”ን እያንጎራጎሩ ስለመሆናቸው ጠርቶ ከሚሰማው ድምፃቸው መረዳት አይገድም፡፡ የግብፃዊያንን፤ የቱኒዚያዊያንን፤ የዩክሬናዊያንን….አብዮታዊ ድል እያወደሱ ወደፊት የሚያገሰግሱ፤ አደባባዩን በንቃት የሚያማትሩ…. የለውጥ ጥያቄ ያነገቡ አዳዲስ ከዋክብት መፈንጠቃቸውን ጆሮዬ እየሰማ፤ ዓይኔም እያየ በመሆኑ ልቤ በደስታ ሙቀት መሞላቱን ስመሰክር በኩራት ነው፡፡
ጓዶች ሆይ፦ ገዥው-ግንባር ዛሬም እንደትላንቱ በ“ምርጫ” ስም የጭቆና ዘመናችንን ለማራዘም የማይፈነቅለው ቋጥኝ፣ የማይንደው ጋራ፣ የማይገባባት ጉድጓድ እንደሌለ በትዝብት እየተመለከትን ነው፡፡ በድርጅታዊ መዋቅሩ ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠረው ምርጫ ቦርድ ፊት-አውራሪነት፤ በካድሬዎቹ ታዛቢነት፤ በጭፍራ “ተቃዋሚ“ ድርጅት አጃቢነት ለአምስተኛው ክሹፍ ምርጫ ነጋሪት እየጎሰመ መሆኑንም እያስተዋልን ነው፡፡ አልቃሻ የፖለቲካ አቋም የተጠናውታቸውን ጨምሮ ራስ-ወዳዶችና ለዘብተኞችን ከጎኑ ማሰለፉ ፍንትው ብሎ የሚታይ ኩነት ሆኗል፡፡ ይህ ሽር-ጉድ በፍፁም ልባችን የምንታመንለትን የ“ህዳሴ (ሦስተኛው) አብዬት”ን ለመቀልበስ ቀን ከሌት እያሴሩ ስለመሆኑ ይነግረናል፡፡
ርግጥ ነው፣ ሥርዓቱ ከሁለት አስርታት በላይ ያለመንገራገጭ መሰንበት የቻለው እንዳሻው በማሰሩና በዘፈቀደ በመግደሉ ብቻ አይደለም፤ መስዋዕትነትን ከሚጠይቅ ትግል ይልቅ አፋዊነትን በሚመርጡ የተቃውሞ ስብስብ ስሁት ስልትም ጭምር እንጂ፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ይህ የትላንት ታሪክ ዛሬም ሊደገም ከደጅ ያለ መስሏል፡፡ በሃሳውያን የአመራር አባላት ቁጥጥር ስር የዋሉት ፓርቲዎችም የአገዛዙን የፖለቲካ ንቅዘት መተቸት ስለቻሉ ብቻ በ“ብርቱ” እየሰሩ መስሏቸዋል፡፡ ዘመኑን የሚመጥን አማራጭ የትግል መንገድ ከመከተል፤ ከቤተ-መንግስት የሚወረወርላቸውን ጥቂት የ“ምክር ቤት” ወንበርን በተስፋ መጠበቅ አብዝተው መርጠዋል፡፡ ለወይኑ ዛፍም የእጅ ስንዝር ያህል ርቀት የቀራቸው በማስመሰል ደጋግመው አታለውናል፤ ያለአንዳች ድርጅታዊ ስራ በምርጫ ለመሳተፍ ተዋክበው አዋክበውናል፤ ስተው አስተውናል፡፡ በ“ውድድሩ”ም ቀደሞውኑ የተገመተውን ሽንፈት ሲከናነቡ፤ በ“ተጭበርብረናል” የጓዳ መግለጫ ከመቃወም የዘለለ ሳይራመዱና ከታሪካዊው ስህተታቸው ሳይማሩ በቀጣዩም ለመሳተፍ ቅንጣት ሲያንገራግሩ አይስተዋሉም፡፡ ስለምን ቢሉ? “ምርጫ“ የምትለውን ቃል ነክሰው ከተከተሩ ሀያ አራት አመታትን አስቆጥረዋልና ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ፣ የአውሮፓ ህብረት የዘንድሮውን ምርጫ እንደማይታዘብ ይፋ ባደረገበት አቋሙ ያስተላለፈውን መልዕክት ወርቁን-ከሰሙ ለይተው መረዳት ተስኗቸዋል፡፡ መቼም ኃይለማርያም ደሳለኝ “በበጀት እጥረት ነው” ሲል ማሾፉን ከቁም-ነገር ከወሰዱት የክ/ዘመኑ ታላቅ ስላቅ መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈም አንድን ምርጫ ዲሞክራሲያዊ የሚያሰኘው በነፃ ውድድር ላይ ሲመሰረት፣ ዜጎች ሁሉ ያለ ተፅዕኖ በፖለቲካው ላይ መሳተፍም ሆነ የሚምኑትን ያለፍርሀት መናገር ሲችሉ፤ እንዲሁም ከምርጫው በኋላ የህዝብን አለቃነት የሚቀበል መንግስት መመስረቱ ሲሳካ መሆኑን ለመረዳት ከፖለቲካ ሀሁ የዘለለ እውቀት አለመጠየቁ ከማንም የሚሰወር አይደለም፡፡ ይህን ለመረዳት ያልተዘጋጀ ግን በመጪው “ዲሞክራሲያዊና ፍትሀዊ” ምርጫ ላይ ይሳተፋል፡፡
የሆነው ሆኖ ወደር በማይገኝለት ጥልቅ ብሶት የሰመጠ እና የሥርዓታዊ ምሬትን የመጨረሻ ፅዋ አንጠፍጥፎ የጨለጠ ህዝብ ከእሳተ-ጎመራ የሚልቅ፤ አንደዕቶን የሚንቀለቀል የቁጣ ስሜት ስለማርገዙ ለመመስከር ኮኮብ ቆጣሪ ማፈላለግን አይጠይቅም፡፡ በየግንባራችን ላይ የተቸከቸከው ብሶት-ወለድ ጉርምርምታ የአመፁ ቀናት በቅርብ ስለመሆናቸው ያስረግጥልናል፡፡ ዘመን ተጋሪዎቼም ርቱዕ ፍትህንም ሆነ የዜግነት ክብርን ከህዝባዊ እምቢ-ተኝነት እንጂ ከኮሮጆ ሊያገኙት እንደማይችሉ ካለፉበት የታሪክ ምዕራፍ ከተረዱ ሰነባብተዋል፡፡ ቅዱስ መፅሀፉም “ህግ ከሌለ ህግን የመተላለፍ በደል አይኖርም” እንዲል፤ ሥርዓቱ ከጭቆና ማራዘሚያነት በዘለለ ዋጋ በማያወጡት ቅምጥ ፍርድ ቤቶቹ በኩል እንደፈለገው የሚመነዝራቸውንና ንፁሃንን ለግፍ እስር ወህኒ የሚወረውርባቸውን የህግ አንቀፆች በእንዲህ አይነቱ ንቅናቄ ወቅት በግላጭ መጣሱ የትግሉ ቅዱስ ግዴታ መሆኑን ለማስታወስ እወዳለሁ፡፡ በርግጥ ከለውጡ ቀድሞ በሚኖረው ነውጥ ጥቂቶችን ማሰር ይቻል ይሆናል፡፡ ይህ ግን ትግሉንም ሆነ ድሉን አያቆመውም፡፡ በ1960ዎቹ አጋማሽ ታዋቂው የጥቁሮች መብት ተሟጋች አሜሪካዊው ማርቲን ሉተር ኪንግ በመኖሪያ ቤቱ ላይ የተቃጣበትን የግድያ ሙከራ ተከትሎ በደጁ ለተሰበሰቡት እንዲህ ሲል መናገሩን ታሪክ መዝግቦልናል፦ “እኔን ብታስሩኝ እንኳን ትግላችንን ማቆም አትችሉም፡፡ ምክኒያቱም የምንሰራው ትክክል የሆነ ሥራ ነውና አምላክም ቢሆን ከእኛ ጋር ነው”
ጓዶች ሆይ፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ! ጥቂት ወራት የቀረውን የይስሙላ ምርጫ ረስተን፤ እጅ ለእጅ ተያይዘን በባንዲራችን ሕብረ-ቀለማት አሸብርቀን ይህን የተጠላና በክፋቱ ወደር የማይገኝለትን ጨቋኝ-ሥርዓት በሰላማዊ አመፅ ለማስወገድ፤ እሳት በሚተፉ አንደበቶቻችን አደባባዩን ከማንቀጥቀጥ የተሻለ አማራጭ የለንም፡፡ በጩኸት የፈረሰችው ኢያሪኮ ብቻ ሳትሆን የዛሬውም አገዛዝ ስለመሆኑ ለዓለም የምናውጅባቸው ቀናት እጅግ ቅርብ ናቸው፡፡ ከነማርቲን ጋር የነበረው አምላክም ከተበደለው ህዝብ ጎን ይሰለፋል፡፡ ያኔም የሞትንላቸውና የታሰርንላቸው ጥያቄዎቻችን ጥያቄ መሆናቸው ያበቃለታል፡፡ በድላችን ማግስት ምላሽ አግኝተው ታሪክ ይሆናሉ፡
እስከዚያው ግን የነካኩትን ሁሉ በልቶ የጨረሰ ሥርዓት ቀጣይ ባለተራ የሚያደርገው ለዘብተኞችን እና “ምን አገባኝ” ባዮችን መሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡ ይህን ሁኔታም ከእኔ ደካማ ቃላት ይልቅ የባለቅኔው ሥንኞች የበለጠ አብራርተውታልና ጥቂት ቀንጭቤ ላብቃ፦

“ዝም ኣልኳቸው ዝም ይበሉኝ
ትቻቸዋለሁ ይተውኝ
አልነካቸውም አይንኩኝ

ብለህ ተገልለህ ርቀህ
እውነት ይተውኛል ብለህ
እንዴት ተስፋ ታደርጋለህ?!….

….የህሊናህ ሚዛን ረግቶ…
ጉዳዩ ሁሉ ኩልል ሲል
የደፈረሰው ሲያጠልል
እግዜር ያሳያችሁ ብለህ ፍረዱኝ እንዳትል
ከናካቴው ሳይጨርስህ
ምንም ቢሆን ሰላም አይሰጥህ”


ኢትዮሚድያ – Ethiomedia.com

Ethiopia refuses allow access to imprisoned British citizen

February 8, 2015

(THE INDEPENDENT) Ethiopia has refused to allow a delegation of parliamentarians to visit a British dissident facing the death penalty in the African country.Andargachew Tsige, beloved Ethiopian opposition leader
Andy Tsege, who is the secretary-general of a banned Ethiopian opposition movement, was sentenced to death at a trial held in his absence in 2009.  He was travelling from Dubai to Eritrea last June when he disappeared during a stopover in Yemen, in what campaigners regard as a politically motivated kidnapping. Weeks later, he emerged in detention in Ethiopia.
A delegation led by Jeremy Corbyn, Mr Tsege’s constituency MP, was to visit Ethiopia in a bid to secure his release. But the trip was abandoned after a meeting with Ethiopian ambassador Berhanu Kebede in London last week.
Mr Corbyn told The Independent: “We had made plans to go and see him next weekend and they said we would be refused admission to the detention facility.”
Lord Dholakia, the vice-chairman of the all-party parliamentary group on Ethiopia, who was due to travel out with Mr Corbyn, said it was made clear that they would not be welcome. Mr Corbyn is demanding that the Ethiopian government allows Mr Tsege’s lawyer, Clive Stafford-Smith, the director of Reprieve, to visit him and will raise the issue in the Commons this week. The Ethiopian embassy in London has accused Mr Tsege – who came to Britain as a political refugee in 1979 – of being a member of a “terrorist organisation” which wants to “overthrow the legitimate government of Ethiopia”.
A spokesman for the Ethiopian embassy said: “The ambassador advised the parliamentarians that there was no need for them to go to Ethiopia as the case is being properly handled by the courts.”
Last night, Yemi Hailemariam, Mr Tsege’s partner and mother of their three children, accused the ambassador of being “a mouthpiece for his bosses who have no regard for basic human rights”. Mr Tsege’s family will go to Downing Street today – which is his 60th birthday – to hand in a petition calling on David Cameron to demand his return. It can also be revealed that the Foreign Office minister Tobias Ellwood broke a promise to Mr Tsege’s family that his case would be raised during the African Union summit in Ethiopia last month.
Mr Ellwood had pledged that senior officials would raise the case. But in an email sent to Ms Hailemariam last week, a government official admitted: “Access to Ethiopian ministers is extremely limited during the summit and so it wasn’t possible to have a bilateral meeting with senior officials who might have influence over the case.”
A spokesman for the Foreign Office said: “We remain deeply concerned about Ethiopia’s refusal to allow regular consular visits to Mr Tsege and his lack of access to a lawyer, and are concerned that others seeking to visit him have also been refused access.”

ecadforum.com/

Saturday, 7 February 2015

ኢህአዴግ በጋራ ንቅናቄው መንበርከኩን አመነ!

“አሜሪካ በህወሃት/ኢህአዴግ ላይ ፖሊሲዋን ልትቀይር ይገባታል”

obang metho1

* ኢንቨስተሮች “የደም ከፈን” ላለመግዛት ወሰኑ

በኦሞ ሸለቆ ድሆችን ከመሬታቸው በማባረር የሚያመርተውን ጥጥ ወደ ውጭ ለመላክ ከስምምነት ደርሶ የነበረው ኢህአዴግ ባለፈው ሰሞን ያልጠበቀው ምላሽ ደርሶታል፡፡ ምላሹን ተከትሎ የጥጥ ግብይቱ የጨነገፈው በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) መሆኑን በገሃድ አመነ፡፡ በኢህአዴግ ስትራቴጂክ በሆኑ ቁልፍ አካሄዶች ላይ አስቀድሞ የመልስ ምት በመምታት ፈተናው ውስጥ የከተታቸው አኢጋን እና መሪው ኦባንግ ሜቶ መዋቅራቸው ሊገኝ አለመቻሉ ኢህዴግን እንዳስጨነቀው ተሰማ፡፡ ኦባንግ ሜቶ በሰማሁት ተዝናንቻለሁ ብለዋል፡፡ በዛሬው ዕለት አቶ ኦባንግ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ አሜሪካ መከተል የሚገባትን አካሄድ በመዘርዘር ለፕሬዚዳንት ኦባማ ፖሊሲ ሊያስቀይር የሚችል ደብዳቤ ልከዋል፡፡
ኢህአዴግ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ በቦታቸው ላይ ጥጥ እያበቀለና ጨርቅ እየሰፋ ለምዕራባዊ ኩባንያዎች ለመቸርቸር የገባውን ውለታ ያጠፉበት ሁለቱ ኩባንያዎች ዓለምአቀፋዊው የስዊድን ጨርቃ ጨርቅ ሻጭ ኤች ኤንድ ኤምና የጀርመኑ ቼቦ ናቸው፡፡ ባለሃብቶቹ ከኦሞ ሸለቆ ሰብዓዊ መብታቸው እየተገፈፈ መሬታቸው በተነጠቀባቸው ዜጎች መኖሪያ ላይ ጥጥ ተመርቶ የሚፈበረከው ጨርቃጨርቅ “የደም ከፈን” አድርገው በመቁጠር ስምምነታቸውን መሰረዛቸውንና ውሉ መጨናገፉን ያመኑት የኢህአዴግ ጨርቃ ጨርቅ ተቋም የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ባንተ ይሁን ገሠሠ ለሪፖርተር ባለፈው ሰሞን በተናገሩበት ወቅት ነው፡፡
የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ነን ባዮች” በማለት የንግድ ስምምነቱ ውል ቀለሙ ሳይደርቅ፤ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ድርጅት በጉዳዩ ላይ ሃሳብ ሳይሰጥ፣ በተቋም ደረጃም ይሁን በፖለቲካ ፓርቲ መግለጫ ሳይሰጥበት፣ በአገር ውስጥም ይሁን በተለይ በውጭ የሚገኙ “አክቲቪስቶች” ድምጻቸውን ሳያሰሙበት ጉዳዩን የራሱ አድርጎ በቀጥታ ለኤች ኤንድ ኤምና ለዋና ሥራ አስፈጻሚው “የደም ከፈን” በማለት ኩባንያው ራሱን ከዚህ ዓይነት እርም የተላበሰ ስምምነት እንዲያጸዳ ማስጠንቀቂያ የላከው አቶ ኦባንግ የሚመሩት አኢጋን ነበር፡፡
ይኸው በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ጥቁሩ ሰው” ተፈርሞ የተበተነው የማስጠንቀቂ ደብዳቤ ቅድሚያ የተዘገበውም በዚሁ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ነበር፡፡ ይህ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ኤች ኤንድ ኤም ሲደርሰው በወቅቱ “በመልካም የንግድ ተግባር” ዓለምአቀፋዊ ሽልማት በዋሽንግተን ዲሲ የሚቀበልበት ወቅት ላይ ነበር፡፡ በወቅቱ የጋራ ንቅናቄው ለኤች ኤንድ ኤም ከጻፈው ደብዳቤ በተጨማሪ ከጀርመኑ ቼቦ ጋር ቀጥተኛ ባልሆኑ መንገዶች በመነጋገርና ተጽዕኖ በማድረግ የፈረመውን ውል በአንክሮ እንዲከታተል ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰው አድርጎ እንደነበር የጋራ ንቅናቄው ለጎልጉል አስታውቋል፡፡
የኢህአዴጉ ሹመኛ ለሪፖርተር ቃላቸውን ሲሰጡ ስም አይጥሩ እንጂ “ነን ባዮች” ሲሉ የገለጹት በቅድሚያ አቶ ኦባንግ የሚመሩትን አኢጋን ስለመሆኑ ጥርጥር እንደሌለ ከአዲስ አበባ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አመልክቷል፡፡ ከዚሁ አዲስ አበባ የተገኘው መረጃ እንደሚመለክተው አቶ ኦባንግ በኢህአዴግ ቁልፍ አካሄዶች ላይ አስቀድመው መረጃ በማውጣትና በማጋለጥ “ደንቃራ” እንደሆኑባቸው ታውቋል፡፡
ለኢህአዴግ ከሚያገለግሉ ቁልፍ ሰዎች መካከል የተገኘ መረጃ እንደሆነ በመጥቀስ እንደተጠቆመው ኢህአዴግ የአቶ ኦባንግን እና አኢጋንን አሠራር እንዲሁም ያለውን የግንኙነት ደረጃ በተጨባጭ ለመሰለል እንዳቃተው ታውቋል፡፡
በተለይ በዳያስፖራው የፖለቲካ ስልጠት (ሲስተም) ያለው የህወሃት/ኢህአዴግ አደረጃጀት ኦባንግ እና ድርጅታቸውን አስመልክቶ የሚሰበስበው መረጃ አቶ ኦባንግ በፌስቡክ ከሚለቁት ብዙም ያልተለየ በመሆኑ ብዥታን ፈጥሮባቸዋል፡፡ በታላላቅ ቦታዎች፣ በከፍተኛ ስብሰባዎች፣ “አንቱ” በሚጠሩ ተጽዕኖ ፈጣሪ ኃይሎች፤ ግዙፍ በሚባሉ የዓለም ተቋማት፣ በታላላቅ መንግሥታት ወዘተ ኢትዮጵያን በብቸኝነት እየወከሉ ፖሊሲ እስከማስቀየር የደረሱት አቶ ኦባንግ “ለኢህአዴግ ራስ ምታት ሆነዋል” በማለት የአገዛዙ ባለሥልጣን መናገራቸውን ከመረጃ ሰዎቻችን ለማወቅተችሏል፡፡
ይህንን አስመልክቶ አቶ ኦባንግ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ “እንዲህ ያለው የኢህአዴግ ስጋት ለእኔ እንደመዝናኛ እቆጥረዋለሁ” ነው ያሉት፡፡ በማያያዝም ድርጅታቸው አኢጋንም ሆነ እርሳቸው ምስጢር የሚባል ነገር እንደሌለው አገር ወዳዶች የሚመሩት፣ የስልኩም ሆነ ማንኛውም የመገናኛ መንገዱ በገሃድ የሚታወቅ፣ በግልጽ ቋንቋ ዘረኝነትን የሚጸየፍ፣ ለሰብዓዊነት የሚቆረቀቆር፣ አጀንዳውም ግልጽ የሆነ፣ በየትኛውም ቦታ የሚገኝ ድርጅት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “ኢህአዴግና አጋር ድርጅቶቹ አኢጋንን አወቃቀሩንና አሠራሩን ለማወቅ ስባሪ ሰከንድ ማባከን የለባቸውም፤ አስፈላጊ ነው ብለው የሚገምቱትን ነገር በሙሉ ቢጠይቁን እንነግራቸዋለን፤ ከሕዝብ ደብቀን የምንሠራው ሥራ የለንም፤ ዘረኝነትን ለመቃወም እና ለማፍረስ፤ ሰብዓዊነትን ከዘረኝነት በፊት በአዲሲቷ ኢትዮጵያ ለማስፈን ለምን ምስጢራዊ ሥራ ያስፈልገዋል? እኛ ለስለላና ለምስጢራዊ ሥራ የምናባክነው ጊዜና ገንዘብ የለንም፤ ይልቁንም የህወሃት/ኢህአዴግ ሰዎች እውነትን ለመጋፈጥ ካልፈሩ በቀጥታ በማንኛውም ጊዜ ሊያገኙን ይችላሉ” በማለት “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያውያን የጥሪ ድምጽ በተሰማመበት ቦታ ሁሉ ቀድመው በመድረስ የሚታወቁት ኦባንግ በስደት እስር ቤት ሲማቅቁ ተረስተው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ከሜክሲኮና ከጃፓን ነጻ በማስወጣት፤ በአውሮጳ አገራት የስደተኛ ጉዳያቸው በህወሃት/ኢህአዴግ ሰላዮችና በሥርዓቱ ቀጥተኛ ተሳትፎ መከራ ውስጥ እንዲገባ የተደረገባቸውን ወገኖች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር የስደተኛ ፖሊሲዎችን በማስቀየር፤ በኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ካሩቱሪና መሰል ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ስም አለአግባብ የነዋሪዎችን መሬት በመንጠቅ የሚያደርሱትን ግፍ በተጠናቀረ ዘገባ መልክ በማውጣት የዓለም ሕዝብ እንዲያውቀው ከማድረግ አልፎ የህወሃት/ኢህአዴግን ፖሊሲ በማጋለጥ ሕንድ ድረስ በመሄድባደረጉት ውትወታ የካሩቱሪን አካሄድ በማስቀየር፤ የዓለም ባንክ ለኢህአዴግ የሰጠው የዕርዳታ ገንዘብ ኢህአዴግ ለወታደሮቹ ደመወዝ መክፈያ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ መከራ እያደረሰ መሆኑን ይህም የባንኩን አሠራር በግልጽ የሚጻረር መሆኑን በማጋለጥና የፖሊሲ አቅጣጫ በማስቀየር፤ ወዘተ በዳያስፖራ ከሚገኙት ድርጅቶች በተለየ መልኩ የሚንቀሳቀሱት አቶ ኦባንግ ሜቶና ድርጅታቸው ሲሰራ ብዙ ባይዘፈንለትም ውጤት በማስመዝገብ ግን “ወደር እንደማይገኝለት” ኢትዮጵያ ድረስ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦች ይመሰክሩለታል፡፡
የደም ከፈን” አልገዛም ያለውና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ የልብስ መደብሮች ያሉት የስዊድኑ ኤች ኤንድ ኤም ድርጅት ስመጥር ኩባንያ እንደሆነ መረጃዎች ይናገራሉ፡፡ የጀርመኑ ቼቦም በተመሳሳይ ሁኔታ እንደሚጠቀስ ይታወቃል፡፡ ጎልጉል ባለው መረጃ መሠረት የንግድ ስምምነቱ የጨነገፈው ከጥጥ ማምረት ጋር በተያያዘ ሳይሆን በአካባቢው ያለው የሰላም መደፍረስ፣ የሕዝብ እምቢተኝነት ማየል፣ የግፍ መባባስ ዝርፊና ቅሚያው ከልክ እያለፈ መሄድ ከአካባቢው ሙቀት ጋር ተዳምሮ “ለባለሃብቶቹ” ሰላም የሚሰጥ ኢንቨስትመንት ባለመሆኑ ነው፡፡ የተለያዩ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ከዚህ በፊትም ጎልጉል በተለያዩ ጊዜያት አስቀድሞ እንደዘገበው በኦሞ ሸለቆና በምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢ ያሉ ታላላቅ ኢንቨስትመንቶች እያደር መጨናገፋቸው የማይቀር እንደሆነ በስፋት ይታመናል፡፡ የተፈጥሮን ደን በማውደም ጣውላ ሲቸበችቡ የነበሩት “ኢንቨስተሮች” እንኳንስ ሊያለሙ የተበደሩትን መክፈል አቅቷቸው እያቃተቱ መሆናቸውን በቅርቡ ኢህአዴግ እያመነ መሆኑን በራሱ በኢህአዴግ አፍ ተመስክሯል፡፡
አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት “በጥምባሆ መግዣ ዋጋ መሬት እየቸበቸበ፣ ምስኪን ንጹሃንን እያፈናቀለ፤ ምነው ያሉትን እያሰረና እየገደለ፣ “አገር አደገች፤ ተመነደገች፤ ልማት ነው፤ ሥራ ላይ ነን” የሚለው ኢህአዴግ፤ ሸራተን በውስኪ አጅቦ ያወጀው ኢንቨስትመንት መጨረሻው ይኸው ነው፡፡ በአበባ እርሻ ላስቲክና ካርቶን የባንክ ዋስትና (ኮላተራል) አድርገው የአገሪቱን ባንክ አልበው የሄዱትን አጭበርባሪ ድርጅቶችና አጋሮቻቸውን ልማት ባንክና ህወሃት ያውቋቸዋል፡፡ ይህ ቀን ጠብቆ ሕዝብና ትውልድ ፍርድ የሚሰጡበት ነው” ብለዋል፡፡ በምዕራብ ኢትዮጵያ በተለይ በጋምቤላ አካባቢ በትንሹ ከ70 በመቶ በላይ “ባለሃብት” ተብለው መሬት የወሰዱት የትግራይ ነዋሪዎች ከኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት የተገኘው ይፋዊ መረጃ ያረጋግጣል፡፡
በሌላ በኩል የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ አሜሪካ ህወሃት/ኢህአዴግን ይዛ የትም መድረስ እንደማትችልና ይልቁንም የሕግ የበላይነት እንዲከበር ፖሊሲዋን ልትመረምር እንደሚገባ በማሳሰብ ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ደብዳቤ ልከዋል፡፡ በተለይ መጪውን ምርጫ ተያይዞ ህወሃት/ኢህአዴግ የሚከተለውን የአፈና ፖሊሲ የምርጫውን ውጤት አስቀድሞ የሚተነብይ መሆኑን አቶ ኦባንግ በደብዳቤያቸው ማስረጃዎችን በመጥቀስ ዘርዝረዋል፡፡ ከዚህ ጋር በማያያዝ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ላይ ምርጫ ቦርድ የወሰደው ዕርምጃ ተጠቃሽ መሆኑን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ አስታውሰዋል፡፡
ስለሆነም ምህዳሩ እንዲሰፋ፣ አፈናው እንዲቆም፣ ምርጫ ቦርድ ያለአድልዎ መስራት እንዲችል፣ የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ያረቀቁት “ኦምኒበስ ረቂቅ 2015” ተግባራዊ እንዲሆን፣ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ እንዲሁም ቁልፍ በሆኑ የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ላይ ወደ አሜሪካ የመግባት ዕቀባ (የበረራ ማዕቀብ) እንዲጣልባቸውና በውጭ አገር ያከማቹትን ገንዘብና ሃብት እንዳይንቀሳቀስ እንዲደረግ፣ ወዘተ አሜሪካ የፖሊሲ ለውጥ እንድታደርግ ለፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል፡፡ ኦባንግ ይህንን ያቀረቡት በልመና መልክ ወይም “ያለ አሜሪካ እርዳታ አይሆንልንም” በማለት መንፈስ ሳይሆን የኢህአዴግን የበጀት ኮሮጆ በመሙላትና “አሸባሪዎችን ለመዋጋት” በሚል ድጋፍ በመስጠት ቀዳሚዋ አሜሪካ በመሆኗ ከግብር ከፋይዎቿ እየሰበሰበች በምትሰጠው ገንዘብ ሕዝብ እንዳይበደል፣ እንዳይሰቃይ፣ እንዳይገደል፣ መብቱ እንዲከበር፣ ነጻነት እንዲያገኝ፣ ወዘተ የማድረግ የሞራል ግዴታ ስላለባት ነው፡፡ የአቶ ኦባንግ ደብዳቤ ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይነበባል፡-

An Open Letter to President Barack Obama,

The alarming political conditions in Ethiopia that may threaten the future security and stability of this strategic country in the Horn of Africa
February 5, 2015
Honorable Barack Obama
The President of the United States of America
The White House
1600 Pennsylvania Avenue
Washington, DC 20501
Dear President Obama,
I am writing this to you on behalf of the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) to alert you to the alarming political conditions in Ethiopia that may threaten the future security and stability of this strategic country in the Horn of Africa. Current United States policies that strongly support the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) are being abused by this regime to undermine the democratic aspirations of the Ethiopian people. As the EPRDF intensifies the crack down on the political and human rights of the people there is fear that some event may ignite the simmering tensions, causing them to explode into violence, killing and chaos.
My name is Obang Metho. I am the Executive Director of the SMNE, a non-violent, non-political grassroots social justice movement representing the diverse people of Ethiopia.
I come to you first and foremost as a human being who believes that the future well being of our global society rests in the hands of those among us who can put humanity before ethnicity or any other distinctions that divide and dehumanize other human beings from ourselves; inspiring us to care about these others; not only because of the intrinsic God-given value of each life, but also because none of us will be free until all are free. These are the underlying principles of the SMNE. The SMNE is committed to bringing truth, justice, freedom, equality, reconciliation, accountability, respect for human and civil rights and economic prosperity to the people of Ethiopia and beyond.
Urgency of concern:
The escalation of frustrations regarding the upcoming Ethiopian national elections scheduled for May 24, 2015, may become the trigger to violence as Ethiopians face the dismal reality that all avenues to democratic political change are solidly blocked. If violence breaks out, it may spin out of control. Now is the time to take steps to avoid it; however, the TPLF/EPRDF fears the people to the degree that they may find it impossible to alter their direction, even if it is what pushes people over the edge towards a violent backlash. The SMNE seeks to help all parties avoid such an outcome.
Unfortunately, the TPLF/EPRDF will never voluntarily give up power by holding a free and fair election. They know opening up political space would lead to a reversal of power. As a result, there is little hope that the situation will improve without leverage.
We know that, the United States is the chief financial, political and security backer of the TPLF/EPRDF. If the appropriate actions are taken, it may give the US an opportunity to improve the long-term interests of the US in Ethiopia and the Horn as well as to contribute to a better future for Ethiopians and their neighbors.
Clearly, Ethiopia is the most stable country among its neighbors like Eritrea, Somalia, Sudan and South Sudan, but if it were to descend into instability, it would be devastating for the Horn of Africa and beyond. There needs to be an alternative that would offer a peaceful way out for all parties, including the TPLF/EPRDF. The TPLF/EPRDF will not and cannot do it alone. The people of Ethiopia must do the major work, but if they are facing a strongly-US, UK or EU-supported TPLF/EPRDF; the job will be all the more difficult.
The TPLF/EPRDF has become an increasingly totalitarian government over the last 24 years they have been in power; however, the real power behind them is the ethnic-based Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF) that dominates every branch of the government. Their stated goal is to gain perpetual rule and hegemony of Ethiopia. As documented by both the US Embassy in Addis Ababa and the US State Department’s human rights division, the Ethiopian government is becoming increasingly brutal in its crack down on basic freedom, democratic processes, and the rule of law. This is not new.
Since coming to power, this regime has never held a free and fair election. The closest it came to allowing a degree of political space was in 2005 when the opposition nearly won. Instead, the TPLF/EPRDF claimed a victory, killed 193 election protestors in the streets, imprisoned opposition members, and closed down all political space in the 2010 election. At that time they even misused humanitarian aid to control voting at every level; finally claiming an absurd 99.6% electoral victory. The Ethiopian Parliament has only one opposition member out of 547.
Some are willing to overlook the lack of democratic progress, believing that claims of economic progress make up for it. However, although there may be some advances made, TPLF/EPRDF statistics claiming double-digit economic growth are being challenged as Ethiopians remain at the bottom of most every poverty index. There is little to no private sector, but instead, economic opportunities are limited to regime cronies, another source of contention among Ethiopians.
A robust civil sector that could act as watchdogs of society has been eliminated due to the implementation of the Charities and Societies Proclamation. This is a law that has made it a crime for civic organizations who receive more than 10% of the funding from foreign sources to advance human and democratic rights, to promote equality among ethnicities, genders and religions, to promote rights for the disabled and children, to promote conflict resolution or reconciliation, or to promote the efficiency of justice and law enforcement services. Some 2,600 or more civic organizations closed in response. In their place, the TPLF/EPRDF has set-up pseudo-organizations they control.
Similarly, they have passed an Anti-Terrorism Law that is used to silence democratic voices, journalists, bloggers, editors, opposition leaders and religious leaders under false pretenses. Ethiopia has become one of the highest jailers of political prisoners in Africa. In present day Ethiopia, every important public and private institution is under the control of the TPLF/EPRDF, whether it is the judiciary, the police and security forces, government offices and ministries all the way to the local level, the military, the media, the telecom system, the Internet, the educational system, the economy, and most importantly right now, the National Election Board of Ethiopia (NEBE).
In the last month, they have increased their efforts to eliminate any competition. This includes beating up opposition leaders and any who speak out against them, even pregnant women and the elderly. Many are jailed in an effort to intimidate any who call for a legitimate democratic process. Obstacles are erected to block every effort of opposition parties to satisfy the impossible requirements of the NEBE.
Two prominent opposition political parties, the Unity for Justice and Democracy (UDJ) and the All Ethiopian Unity Party (AEUP), have both made valiant attempts to comply with unreasonable demands; however, they now have been denied participation in the election. Instead, the TPLF/EPRDF has hijacked the ownership of these parties, even taking on their names, UDJ and AEUP. They have appointed their own people to run as candidates against others in the TPLF/EPRDF, essentially competing with themselves in a ruse to confuse the people.
Recommendations for meaningful US action regarding Ethiopia:
US silence or only symbolic gestures regarding the evolving crisis in Ethiopia may work for the short-term, but no one knows for how long. In fact, continued US support or meaningless action may inadvertently exacerbate the crisis and undermine stability. Instead, the US should use their leverage to bring democratic change and sustainable stability to the country; both of which would enhance long-term US interests in Ethiopia and the Horn.
Meaningful actions include:
  • Calling for an independent election commission
  • Implementing the Omnibus Bill 2015 concerning Ethiopia
  • Releasing imprisoned political prisoners
  • Freezing security cooperation with the regime
  • Implementing travel bans on key regime officials and freezing their assets
It is not in the interests of anybody to wait for an explosion. Ethiopia is in crisis. Our goal is to bring peace even as some are beating the drums of violence. We strongly encourage you to put pressure on this regime. Condemn these actions. The US should not be silent when such a stance could contribute to the future wellbeing and stability of this strategic country of over 90 million people.
Respectfully yours,
Obang Metho,
Executive Director of the SMNE
910- 17th St. NW, Suite 419
Washington, DC 20006
Email:Obang@solidaritymovement.org.
Website: www.solidaritymovement.org
This letter has been Cc to
Vice President Joseph Biden
Secretary of State John Kerry
National Security Advisor Susan Rice
Senior Director for African Affairs on the National Security Council Gayle Smith
Senior Director for Democracy on the National Security Council Linda Thomas-Greenfield
Assistant Secretary of State for the Bureau of African Affairs Earl Gast

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!


የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!

Feb 05, 2014
ህወሓት ንፁሀንን ለመደብደብ የሚያበቃ በቂ ክፋት ያለው ልዩ ጦር ሲያሰለጥን ቆይቷል። ይህን ልዩ ጦር የፓሊስን መለያ እያለበሰ ነውረኛ ሥራዎችን እንዲሠራ በማድረግ በአንድ በኩል ንፁሀንን የመጉዳት በሌላ በኩል ደግሞ ፓሊስን በሕዝብ የማስጠላት መንታ ግቦችን ለማሳካት ተጠቅሞበታል። ይህ ልዩ ጦር በአለፉት ጥቂት ሳምንታት ባዶ እጃቸው ለተቃውሞ በወጡ ነብሰ ጡር ሴቶች ላይ ሳይቀር ባሳየው ጭካኔ፣ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ባደረሰው ድብደባ መጠን እና ባካሄደው የግለሰብ ንብረቶች ዝርፊያ የሥርዓቱ ባህርይ ፈጽሞ ከሰውኛ ተፈጥሮ እየወጣ እንደሆነ አመላካች ነው። በእነዚህ ድብደባዎች ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስባቸው ተደርጓል። በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት የተደረገው በደብዳቢዎቹ የግል ውሳኔ ሳይሆን ከበላዮቻቸው በተሰጠ ትዕዛዝ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
በአርበኞች ግንቦት 7: እምነት መሠረት የፓሊስ ከፍተኛ አዛዦች ህወሓቶች ቢሆኑም አብዛኛው የሠራዊቱ አባል በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ የተማረረ፤ የሥርዓቱ መለወጥ የሚፈልግና ሥርዓቱን ለመለወጥ የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ኃይል ነው። ስለሆነም ህወሓት የተለየ ጦር አሰልጥኖ የፓሊስ ልብስ በማልበስ ነውረኛ ወንጀል በማሠራት ፓሊስን ለማስጠላት የሚያደርገው ሴራ ሊጋለጥ ይገባል ብሎ ያምናል። የፓሊስ ሠራዊት አባላትም በስማቸውና በደንብ ልብሳቸው የሚደረገውን ደባ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንዲያጋልጡ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ህወሓት እንደሚያስበው እና የኢትዮጵያም ሕዝብ እውነት አድርጎ እንዲቀበለው እንደሚፈልገው የትግራይ ሕዝብ በጅምላ የህወሓት አፍቃሪና ደጋፊ አይደለም። እንዲያውም በተፃፃሪው ህወሓት ከትግራይ ተወላጆች ልብ እየተነቀነ ነው። የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን/ደምህት) ከትግራይ የበቀለ፤ ህወሓትን በአመጽ ለመፋለም የቆረጠ ኃይል ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በትግራይ ውስጥ ብዙ ደጋፊዎች ያሉት መሆኑ የምናውቀው ሀቅ ነው። አረና ትግራይ ህወሓትን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተነሳ ተሰሚነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ እና አቶ አብርሀ ደስታን የመሰለ ወጣት ኢትዮጵያዊ የፓለቲካ መሪ ያወጣ ድርጅት ነው። ህወሓት አንድነት ፓርቲ ላይ የመረረ አቋም ከወሰደባቸው ምክንያቶች አንዱ በትግራይ ውስጥ ያለው ተቀባይነት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ነው። ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ ለማጣላት የሚያደርገው ጥረት ማክሸፍ ይኖርብናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ተግቶ ይሠራል። አርበኞች ግንቦት 7 ከትግራይ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር ፀረ ህወሓት ትግል በትግራይ ውስጥ መቀጣጠል ይኖርበታል ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ትግራይ የህወሓት መቀበሪያ የመሆኗ ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በዘንድሮው የ2007 የሴራ ምርጫ አማካይነት ተድበስብሰው የመጡ እነዚህ ሁለት ክፋቶች ማለትም ፓሊስን በሕዝብ ማስጠላት እና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የዲሞክራሲ ወገንተኞችን ለይቶ ማጥቃት ከበስተጀርባቸው ያዘሉት እኩይ ዓላማ መጋለጡ መንገዳችን ያጠራልናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። በአንድነትና በመኢአድ የተፈፀው የድርጅትና የንብረት ዘረፋም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኝ ግልጽ ነው፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር በሰማያዊ ፓርቲም ላይ ይፈጽም ይሆናል።
በመሆኑ ከ2007 የሴራ ምርጫ ትሩፋቶች በትግራይ ሕዝብና በፓሊስ ሠራዊት ጀርባ የሚደረገው ደባ መጋለጡ ነው። ይህ ድል ጽኑ መሠረት እንዲይዝ ህወሓትንና የትግራይን ሕዝብ የመነጠል እና ፓሊስ የሕዝብ አጋር መሆኑን የማረጋገጥ ሥራዎችን አጠናክረን መሥራት እንዳለብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !