Friday 15 November 2013

መቋጫ ያጠው የወገኖቻችን ስቃይ እና ሞት በሳውዲ አረቢያ ፡አሁንም ቀጥሏል !

ትላንት አመሻሹ ላይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፍሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን አገርሽቶ በዋለው ተቃውሞ የተጓዳ የሞተ ባይኖርም ኢትዮጵያውያኑ ድምጻቸውን ከፍ አድረገው አንድነን አንድነን … መብታችን ይከበር ….እኛም ሃገር አለን ወዘተ… በሚል መፈክር ታጅበው ብሷታቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን የሚገልጹ የአይን እማኞች የሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመብተን በከፈቱት ቶክስ ይሰማ በነብረው የጥይት ድምጽ አካባቢውን ወደ ጦርነት አውድማ ለውጦት ማምሸቱን የገልጻሉ።


ይህንንም ተከትሎ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ አውቶማቲክ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ተጨማሪ ልዩ ፈጥኖ ደራሽ፡ ኮማንዶዎች ቦታው በመድረስ ተቃውሞውን መግታት ተችሎል ብለዋል ። እንዚህ ምንጮች ትላንት ተቀስቅሷ በነበረው ሁከት ጥቂት ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መደሱን ገልጸዋል። ሰምኑን የሳውዲ አረቢያ መንግስት በውጭ፡ሃገር ነዋሪዎች ላይ ያወጣው ህግ የግዜ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች በኢትዮጵያውያኑ ላይ እየወስዱ ባሉት የተናጥል እርምጃ አያሌ ወገኖቻችን ወደ ሃገሩ ለመምለስ ከየመኖሪያ ቤቱ ነቅሎ አደባባይ ቢወጣም ወደ ሃገር መግባት የሚያስችሉት ነግሮች በመንግስ በኩል ባለመኖሩ ከእልቂት ተርፈው ወደ እስርቤት የተጓጓዙ ከ 20 ሺህ የሚበልጡ ወገኖቻችን በምግብ ወሃ እና የመጸዳጃ ቦታ እጦት እይተሰቃዩ እንደሚገኙ ተግልጾል።

በአንድ ማጎሪያ 4 ቀናቸውን እንዳስቆጠረ የሚነገርለትን ኢትዮጵያዊ እና ሪያድ መንፍሃ ጅዳ እና መካ እስከነ ልጆቻቸው በየመገዱ ፈሶ ቁም ስቅሉን እያየ ያለውን በመቶሺህ የሚቆጠር ወገን ብሷት ለማድመጥም ሆነ ለማየት የመጣ የመግስት ባለስልጣን አለመኖሩ ተገልጾል። ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬ ጅዳ በተለምዶ መስፈላ እይተባለ የሚጠራ አካባቢ በሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች እና በኢትዮጵያውያን መሃከል በተነሳ ግጭጥ 76 ሰዎች መቁሰላቸውን የሚገልጹት ምንጮች በዛ ቀውጢ የቶክስ እሩምታ በጥይት ተደብድቦ የተገደለ ኢትዮጵያዊ ሊኖር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

ተቀማጭነታቸው ሪያድ እና ጃዳ ከተማ በሆኑት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አምባሳደር እና የቆንስላው ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች ላይ ተስፋ የቆረጠው ኢትዮጵያዊ ሰድተኛ እስካሁን በመግስት ወደ ሳውዲ አረቢያ ተጉዘዋል ያለው ለኡካን ቡድን ምንም አይነት የሚጨበጥ፡ነገር ባለምስራታቸው ኢትዮጵያውያኑ ለከፋ አልቂት በመዳረግ ላይ መሆናቸው ታውቋል።ሰሞኑን የውጭ፡ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ክቡር አምባሳደር ዲናሞ ሙፍቲህ ኢትዮጵያውያኑ በሳውዲ አረቢያ እየተፈጸምባቸው ነው የሚባለው የጅምላ ግፍ እና በደል ይሄን ያህል የሚጋግነን እና ቦታ የሚሰጠው አለመሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት ምሽት መንፉአ አካባቢ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ከ 17 በሚበልጥ አውቶብስ ተጭነው የተወሰዱ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ህጻናት ሴቶች አረጋውያን ጨምሮ አያሌ ወገኖቻችን ከሪያድ የ6 ሰአታት ጉዞ በሃላ ያልታወቀ መድረ በዳ የሆነ አካባቢ እንዲወርዱ መገደዳቸውን እና የኢትዮጵያውያኑ እስካሁን ያሉበት ሁኔታ በውል እንደማይታወቅ ተገልጾል።


No comments:

Post a Comment