Sunday 20 December 2015

አዲስ አበባዎች ሊነሱ ነው !

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚከተሉትን መፎክሮች አንግበው መንግስት በአገሪቱ ላይ እየወሰደ ያለውን መንግስታዊ ውንብድና ለመቃወም እየተዘጋጁ መሆናቸው ታወቀ፡፡ የውስጥ ወሬ ምንጮቻችን እነደገለፁት መቸ በይፋ እንደሚጀምሩት በምስጥጢር ተይዝዋል በማለት ክፍለ ሀገር ያሉ(በኦሮሚያ፣በአማራ፣በደቡብ፣…) የተጀመረውን ትግላቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡
ማህበረሰቡ፡- 1. በኦሮሚያና በአማራ እየተደረገ ያለው ደም ማፋሰስ ይቁም!
                2. በልማት ስም ህዝብን ከይዞታቸው ማፈናቀሉ ይቁም!
                3. መሬት የህዝብ እንጂ የመንግስት አይደለም!
                4. የብሄር ፖለቲካ ይቁም! ሆን ተብሎ ብሄርን ከብሄር የማጋጨት ሴራው ይምከን!
                5. መንግስት የከፋፍለህ ግዛው ስትራትጅውን ያቁም!
                6. በርሀብ አለንጋ እየተገረፉ ያሉ ዜጎች አስቸኳይ መፍትሄ ይሻሉ!
                7. የታሰሩ የፖለቲካና የህሌና እስረኞች ይፈቱ!
                8. የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ወደቦታው ይመለስ!
                9. የፍትህ ስርአቱ ይስተካከል!
               10. መንግስት አይን ያወጣ ውሸቱን ያቁም!
               11. መሰረት የሌላቸው መግለጫዎች፣የውሸት ፕሮፖጋንዳዎች፣ዛቻና ማስፈራሪያዎች ይቁሙ! ህዝቡ እውነቱን                          የውቃል! ማንም
 አያምናችሁም!                               
               12. ኢህድግ የሚሰማ ጀሮ፣የሚያይ አይን የለውም! በእብሪት ተወጥሯል!
               13. ኢህድግ የበሰበሰ ድርጂት ነው! ህዝብን ማሰተዳደርና አገርን መምራት ተስኖታል!
               14. ታፍነን አንግዛም፣አባቶቻችን አላወረሱንም!
               15. ዝርፊያው ይቁም!ሙሰኞችና ኪራይ ሰብሳቢዎች ለፍርድ ይቅረቡ!
               16. በጎንደር ዳርቻ ለሱዳን በሚሥጥር የተሰጠው መሬት ይመለስ!
               17. አሸባሪው ህዝብ ሳይሆን መንግሰት ነው!
               18. አሰመሳይ መንግስት ሊሆን አይችልም!
               19. የአንድ ብሄር የበላይነት ይቁም!
               20. መንግስት ውሸት፣ማጭበርበር እና ሌብነትን ባገሪቱ ላይ አንግሷል!
               21. ባገሪቱ ላይ ያሉ አደገኛ እፆች(ጫት፣ሲሻ፣አሸሽ፣…) ይወገዱ! መንግስትም ከማምረት ይቆጠብ!
               22. ህገመንግስቱ ይከበር! አፋኝ ህጎች ይሻሩ!
               23. ህንፃ፣ባቡር፣… ለኛ ምናችንም አይደለም፤በቅድሚያ ነፃነት!
               24. መንግስት የግል ጥቅሙን ትቶ በአገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ የጋራ ውይይት ይጥራ! ከማንኛውም ተቃዋሚ                     ሀይል ጋር ብሄራዊ እርቅ ያካሂድ!
              25. የሽግግር መንግስት ይቋቋም! ፍትሀዊ ምርጫ እንደገና ይካሄድ!
              26. ዳግመኛ ደርግን አናስተናግድም!

ተማሪዎች፣መምህራን እና የመንገስት ሰራተኞች፡-
              1. መንግስት ማህበረሰቡን ማጋጨት ያቁም!
              2. በማህበረሰቡ ላይ የሚደረገው ማዋከብ ይቁም!
              3. ፍታዊ የሀብት ክፍፍል ይኑር!
              4. በአገሪቱ ላይ ወጥ የሆኑ መመሪያች ይኑሩ!
              5. የትምህርት ጥራት ይጠበቅ!
              6. መልካም አስተዳደር እንሻለን!
              7. የታክስ ማሻሻያ ይደረግ!
              8. የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ!
              9. የአርከን ጭማሪ ይፈቀድ!የደረጃ እደገቱ ማሻሻያ ይደረግ!
             10. የውሎ አበል፣የትርፍ ሰአት ክፍያ፣የትራንስፖርት እና የቤት አልዋንስ ይሻሻሉ!
             11. ስራ ቅጥር/ስልጣን በደብዳቤ ሳይሆን በውድድር/በብቃት ይሁን!
             12. መንግሰት የውሸት ድራማ መስረቱን ያቁም!
             13. መንግስት ከመንገድ/ከህንፃ ይልቅ በቅድሚያ ማህበረሰቡን ያልማ!
             14. መንግስት ነጋዴ ነው!
             15. መንግሰት የህዝብ አገልጋይ አንጅ ህዝብ የመንግሰት አገልጋይ መሆን የለበትም!
             16. አገሪቱ “አርቲፊሻል” እድገት ላይ መመስረት የለባትም! ማጭበርበሩ ይብቃ!
             17. ከ2 ጊዜ በላይ ታክስ እየተደረግን ነው! (ደመወዝ ሲከፈል-የስራ ግብር፣እቃ ስንገዛ-ቫት እና የሰርቪስ አገልገሎት፡፡ ስለሆነም 35%+15%+5%=55% ደመወዛችን ታክስ ይደረጋል!)  በቃ! በቃ! በቃ! በቃ! በቃ! በቃ!………………..
እነዚህን መፎክሮች በጋራ በማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እነዳሰቡና መንገስት ለሚወስደው ማንኛውም እንቅስቃሴ እነደማይታገሱትና የመግደል ሙከራ ካደረገም አስፈላጊውን ምላሽ እነደሚያደርጉ ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ አንደሆነ በምሬት ተናግረዋል፡፡ 
 ማንም ሀይል እነደማያደራጃቸው የገለፁ ሲሆን የአመፁ መንስኤ የመንግሰት ብልሹ አሰራር፣አፈና፣ማዋከብ፣ መግደል፣ማፈናቀል፣ግፍ፣አድሎ፣ማሰር፣የኑሮ ውድነቱ፣ፍትህ ማጣቱ፣ብሄርን ከብሄር ማጋጨቱ፣የስነ ልቦና ጫናው ተደማምረው ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት ስለፈጠሩባቸው ከዚህ የባሰ ምን ይመጣል ወይ ሞት ወይ ነፃነት በማለት ከሰፊው የኢትዮጵያ ማሀበረሰብ ተቃዋሚዎችጋር ለመቀላቀል እነደወሰኑ ለወሬ ምነጫችን ተናግረዋል፡፡
የመንግስትን ሀይል ለመቋቋምም ሰላማዊ አመፁ ለሊት ላይ በመጀመር መንግሰትን አከርካሪውን ለመስበር አስበዋል፡፡ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል (ሴት፣ወንድ፣ አዋቂ፣ህፃን፣አረጋውያን፣ የሀይማኖት አባቶች፣መምህራን፣የቢሮ ሰራተኞች፣ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ሹፌሮች፣ነጋዴዎች፣ጎዳና ተዳዳሪዎች፣ተማሪዎች….) ወደ ጎዳና መውጣት የመጀመሪያው የሰልፉ/የአመፁ ምእራፍ ነው፡፡ ማንኛውንም ንብረት ማውደም “በህግ” የተከለከለ
ነው፣ከላይ የተዘረዘሩትን መፎክሮች ማሰማት ብቻ በቂ ነው፡፡ መምህራንና የመንግስት ሰረተኞችም ከሚቀጥለው ሰኞ ጀምረው የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉም አበክረው ገልፀዋል፡፡መቸም ቢሆን ከዚህ በኋላ ትግሉ እንደማይቆም አክለው ገልፀዋል!!
በተጨማሪም ከህዝብ አብራክ የወጣውን ፌድራል ፖሊስንና መከላከያ ሰረዊትን ከጎናቸው እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡
ሼር በማድረግ የትግሉ አጋር ይሁኑ!
ድል ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!!!!!.

Friday 4 December 2015

የወገኖቻችን ስቃይ፣ ችግርና ብሶት በያለንበት ይሰማን፤ ለመፍትሔውም በጋራ እንነሳ!

 የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ


December 3, 2015

በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሰበብ በከተማዋ ዙርያ ያሉ ወገኖቻችንን ማፈናቀል በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ጥቃት ነው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የሚፈናቀሉ ገበሬዎች የሁላችን ወላጆች፣ ወንድሞችና እህቶች ናቸው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የምንፈናቀለው ሁላችንም ነን። ይህን መሰሪ ፕላን በመቃወም ላይ ያሉት የኦሮሞ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።


በዚሁ ወቅት በጎንደር ሌላ አሳዛኝ ጉዳይ ተከስቷል። ህወሓት ከሶስት ሺህ በላይ ዜጎቻችንን ያጎረበት እስር ቤት በእሳት ሲጋይ ዜጎች ተቆልፎባቸው እንዲነዱ ተደርጓል። ከእሳቱ በእድል ያመለጡት በጥይት ታድነዋል። ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ዓይነቱን ጭካኔ የሚያውቁት በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ጊዜ ነው። ይህን ጥቃት በመቃወም ላይ ያሉ የአማራ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።



ግፍ ያልተፈፀመበት የኢትዮጵያ ክፍል ባይኖርም ሰሞኑን በአማራና በኦሮሚያ ላይ በርክቷል። በሁለቱም የአገራችን ክፍሎች የንፁሀን ደም እየፈሰሰ ነው፤ በሁለቱም ቦታዎች የእናቶች ዋይታና እሪታ ጎልቶ እየተሰማ ነው። የህወሓት አገዛዝ የትውልድ ቦታ፣ ቋንቋና ዘር ሳይለይ በኢትዮጵያዊያን ሁሉ ላይ የተደቀነ አደጋ መሆኑ ከምንጊዜውም በላይ ዛሬ ግልጽ ሆኗል።

ለዚህ የምንሰጠው ምላሽ ምንድነው? ዛሬም ኦሮሚያ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የኦሮሞ፤ አማራ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የአማራ ጉዳይ አድርገን እንወስዳለን? መቸ ነው ኦሮሚያ ላይ ለደረሰው ጥቃት አማራዉ፤ አማራ ላይ ለደረሰው ጥቃት ኦሮሞው የሚቆረቆረው?

የሁላችን የጋራ ጠላት የሆነው ህወሓት መኖሩ በዘውግ የተከፋፈለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ አንድነት የሚያመጣ ታላቅ ኃይል ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራና የመጠቃት ወቅት የምንቀራረብበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራ ወቅት በህወሓት ላይ በጋራ የምንነሳበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ዛሬ በኢትዮጵያ ያሉ የተለያዩ ማኅበረሰቦች በሙሉ በፀረ-ህወሓት ትግል መቀናጀት ይኖርባቸዋል። ይህ ማድረግ ግዴታችን ነው።

ለችግሮቻችን መፍትሄ የምናገኘው ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ሆነን ስናስብ እንጂ ችግሮቹ በፈጠሩበት ደረጃ ላይ ቆመን መሆን አይችልም። ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ለመሆን አገር አቀፍ እይታ መኖሩ እጅግ ተፈላጊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያን ሁሉ በተለይም የአማራና የኦሮሞ ልሂቃን ይህንን ጉዳይ አበክረው እንዲያስቡበት አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያሳስባል።

ግፍ ሞልቶ የፈሰሰበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሆኑት ሕፃናት በፌዴራል ፓሊስ ጥይት የሚገደሉበት አሳዛኝ ወቅት ላይ ነን፤ ዜጎች በር ተዘግቶባቸው በእሳት እየጋዩ ነው። ሰፊ እና ለም የእርሻ መሬት ለሱዳን በስጦታነት ለመስጠት ዝግጁቱ የተጠናቀቀበት ወቅት ላይ ነን። 

ከአስር ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተርቧል። በፍትህ እጦት እስር ቤቶች በንፁሃን ዜጎች ተሞልተዋል። ውሀ፣ መብራትና የቴሌፎን አገልግሎት ብርቅ ሊሆኑ ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ግን የሥርዓቱ አገልጋዮችና ደጋፊዎች በህንፃ ላይ ህንፃ እየገነቡ በድሀው ላይ ይሳለቃሉ። የህወሓት አገዛዝ ድህነትን፣ ችጋርን፣ ስደትን፣ የእርስበርስ ግጭቶችን እያባባሰ ኢትዮጵያን እየጋጠ የሚኖር አገዛዝ ነው። 

አገዛዙ በቀደደልን ቦይ ከተጓዝን ችግሮችን ማባባስ እንጂ ማርገብ እንኳን አንችልም። ይህንን ሥርዓት በቃህ ማለት የአማራ ወይም የኦሮሞ አጀንዳ አይደለም፤ ይህ የሁላችንም – የኢትዮጵያዊያን – ጉዳይ ነው።

ለቀምት፣ ሀረር፣ ሱልልታ እና ሌሎች በርካታ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ ለደረሱ ጥቃቶች ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ሀዋሳ፣ መቀሌ፣ አሶሳ፣ ሁመራ፣ ጋምቤላ ውስጥ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በጎንደርና ባህርዳር ለደረሰውም ጥቃት አዳማ፣ ጅማ፣ ሆሳዕና፣ ጅግጅጋ፣ አክሱም ላይ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ለሚደርሰው በደል መላዋን ኢትዮጵያ ሊያሳምም ይገባል። መከፋፈላችን መከራችን አብዝቶታል፤ የህወሓት እድሜን አርዝሟል፤ ይብቃ!

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የመከራ ጊዜዓችን እንዲያጥር በዘውግ ሀረግ፣ በብሔርና እና በሀይማኖትና ሳንታጠር የወገናችን ህመም ይሰማን፤ ተሰምቶንም ለጋራ ትግል እንነሳ ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!