Wednesday 22 April 2015

የህዝባችን ብሶት ይሰማን !

ኢትዮጵያዬ                     22 04 2015

በዛሬው ዕለተ እሮብ  በአዲስ አበባ በአራቱም አቅጣጫዎች  ተጠራርቶ በወገኖቻችን በኢትዮጵውያን ላይ በደቡብ አፍሪካ በህወታቸው ለተቃጠሉት ፣ በሊቢያ እስከ ነፍሳቸው ለታረዱት ፣ በየመን መውጪያና መሸሸጊያ አጥተው የሚደርስላቸው ወገን እና መንግስት ላጡት ወገኖቻችን ፣ በሜድትራንያን ባህር የሻርክ እራት ለሆኑብን ወገኖቻችን  የደረሰብንን ዘግናኝ እና አሰቃቂ ግድያንና አፈናን  ለማውገዝ በተሰበሰበው ህዝብ ላይ ወያኔ መራሹ የኢህዲግ ፖሊስ እና የፌዴራል ፖሊስ  ከህዝቡ ጎን በመቆም ማውገዝ ሲገባቻው በተቃራኒው በዚህ ወቅት በማይጠበቅና በማይታሰብ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ ብሶቱንና የወገኑን ሃዘን እና ጭንቀት ሊጋራ የተሰበሰውን የአዲስ አበባን ህዝብ ላይ ሲተኩሱበት ፣ በአስለቃሽ ጭስ ሲጎዱትና ሲበትኑት ፣ ሲደበድቡ ፣ ሲያፍኑና ሲያስሩ  መገኙታቸው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትና ኢትዮጵያን መሆናቸው የሚያጠራጥር ነው ᎓᎓ ብዙ የአዲስ አበባ ህዝብ በደረሰበት ጉዳት በየመንገዱ ፣ በየቤቱ እና  በየሆስፒታሉ እነደሚገኝም ታውቃል ᎓᎓


 
 
 







የቆማችሁት ህዝብን እነደህዝብ በመሆን ለማገልገልና ለመጠበቅ ነው እንጂ  ላረጀና ለበሰበሰ አምባገነናዊ ስርዓት ግዚያዊ የመገልገያ መሳሪያ ለመሆን አይደለም ᎓᎓ ወቅቱ የለውጥ እነደሆነም ከህዝቡና በአገራችን ህልውና ላይ እየደረሰ ያለውንም እያንዳንዱን ሁኔታም ሳትገነዘቡት እንደማትቀሩ ህሊናችሁ ያውቀዋል ᎓᎓ እናንተ በመታደርሱበት በደል ተማሮ ስንቱ የተሻለ ሃገር ለመሄድ መንገድ ላይ እንደቀረ ቤት ይቁጠረው ᎓᎓ ዛሬም የኢትዮጵያ ህዝብ  በአንድነት ሆኖ ያሳያችሁ እና የነገራችሁ ጭቆናው ይብቃ ! ስደቱ ይብቃ ! የህዝባችን ደም በአሸባሪዎች በከንቱ ፈሶ አይቅር ! ቸነፈሩ ይብቃ ! ዘረኝነቱ ይብቃ ! መታሰሩ እና መገደሉ ይብቃ ! ነፃነትና እኩልነት ለሁሉም ! ሰብዓዊነት ይቅደም ! የመሰብሰብ ፣ የመናገርና የመፃፍ መብት ይከበር ! ሙስና ይብቃ ! መደብለ ፓርቲ ይኑረን ! ካለ አግባብ የታሰሩ የፖለቲካ አመራሮች እና አባላቶች ይፈቱ ! ጋዜጠኞችና ጦማሪያኖች ይፈቱ ! ህዝብ የመረጠው መንግስት ይኑረን ! በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ  በሃሰት የሚለጠፈው የሽብርተኝነት ፕሮፖጋንዳ ይቁም !  ለህዝቦች መሰደድና ስቃይ ተጠያቂው መንግስት ነው !  ፍትህ የበላይነት የሰፈነባት ሃገር ይኑረን !  ልዕልናዋ የተከበረ ዲሞክራሲያት ሃገር ይኑረን ! 

ወቅቱ የግድ የፖሊስ ሰራዊቱና የመከላኪያ ሰራዊቱ ከዘረኝነትና ከፖለቲካ ነፃ የሆነና ለህዝብ ዘብ የቆመ የሀገርን ህልውና የሚያስከብር  መሆኛው ግዜው አሁን ነው ᎓᎓ ህዝብን በማፈን የስልጣንን ግዜ ማራዘም ለአገራችን ኢትዮጵያና ህዝብ ጉዳት እንጂ  ምንም ጥቅም የለውም ! የአንድ ድርጅት ወይም ፓርቲ ጠበቃና አጃቢ መሆን  ይቁም ! መጪውን የለውጥ ግዜ እንደ አንድ ህዝብ እጅ ለእጅ ታያይዘን  የህዝባችንን ክብርና የአገራችንን ህልውና የምናስመልስበት ወቅት ነው !

ክብር ለኢትጵያውያን ! ሞት ለፀረ ኢትዮጵያውያን !

Monday 20 April 2015

በግፍ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን በተመለከተ የአርበኖች ግንቦት 7 መግለጫ

pg7-logo

ሀያ ስምንት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ዛሬ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ደርሷል። ይህ አሰቃቂ መርዶ ልብን የሚሰብር ነው። አይ ሲስ በጥንት በጭለማ ዘመን እንኳን ባልነበረ ጭካኔ ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ሰዎችን በማረድ የሚደሰት፤ በሰው ዘር ሁሉ ላይ የመጣ አውሬ መሆኑን ነብዩ መሐመድ አትድረሱባቸው ያሏቸውንም ኢትዮጵያዊያንን ጭምር በማረድ አረጋገጧል። ይህ አሰቃቂ ተግባር ምንም ዓይነት አመክኖ ሊቀርብለት የማይችል አረመኔዓዊ የሽብር ጥቃት ነው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው አሰቃቂ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል፤ ለሟች ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ይመኛል። ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አይ ሲስን በጥብቅ እንዲያወግዙ፤ በአመቻቸው መንገዶች ሁሉ እንዲታገሉት አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
በዚህ አጋጣሚ የአይሲስን የሽብር ተግባራት ከእስልምና እምነት ጋር ማያያዝ ፈጽሞ ትክክል እንዳልሆነ፤ ብዙሃን ሙስሊሞች የአይሲስና መሰል ቡድኖችን አካሄድ የሚቃመው መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ማስገንዘብ ይሻል። ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ከክርስቲያን ወገኖቻቸው ጋር ተዋደውና ተፋቅረው የኖሩና እየኖሩ ያሉ ሲሆን የሁለቱ ሀይማኖቶች ተከታዮች ተደጋግፎ መኖር ለሀገራችን ህልውና ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ የአርበኞች ግንቦት 7 እምነት ነው።
በያዝነው ሣምንት በወገኖቻችን ላይ እልቂት ሲደርስ የሊቢያ ብቸኛ ክስተት አይደለም። በደቡብ አፍሪቃ ወገኖታችን ከነሕይወታቸው በእሳት ተቃጥለው ተገድለዋል፤ በስለት ተዘልዝለዋል፤ ንብረታቸውን ተዘርፈዋል። በዛሬው ዕለት 700 ዜጎች የሜዲተራኒያን ባህር በጀልባዎች ሲሻገሩ መስመጣቸው ተሰምቷል። በየመን ደግሞ በርካታ ወገኖታችን በጦርነት እሳት ውስጥ እየተማገዱ ናቸው።
ኢትዮጵያዊያን በአገራችን የሰፈነውን የነፃነት እጦት፣ የፍትህ መጓደልና የኑሮ መክበድ ሸሽተን በሄድነት አገር ሁሉ የሚጠብቀን አሰቃቂ ሞትና ውርደት ሆኗል። ኢትዮጵያ ለኑሮ ያልተመቸችን በህወሓት አገዛዝ ብሉሽነት መሆኑ ጥርጥር የለውም። ይህንን ብልሹ አገዛዝ አስወግደን በምንወዳት አገራችን ተከብረን መኖር እንችላለን። ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለ አገር የለም።
አርበኖች ግንቦት 7: የኢትዮጵያዊያን መከራ እንዲያበቃ ስደት ይብቃ ይላል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባሌውና እንደችሎታው በሕዝባዊ አመጽ አሊያም የሥራ ቦታውና መኖርያው ሳይለቅ በሕዝባዊ እምቢተኝነት በተደራጀ መንገድ የህወሓትን አገዛዝን ይታገል። በሕዝባዊ አመጽና በሕዝባዊ እምቢተኝነት የህወሓት ፋሽስቶችን አስወግደን በአገራችን በነፃነትና በክብር እንድንኖር ሀይማኖትም ሆነ የዘር ሀረግ ሳይለየን በጋራ እንታገል የሚል ጥሪ ያቀርባል።
ዘላለማዊ ክብርና እረፍት በግፍ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን

ኢ–ሰብአዊነትንና ሽብርን ደግመን እናውግዝ! ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንታደግ!

ኢ–ሰብአዊነትንና ሽብርን ደግመን እናውግዝ!
ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንታደግ!
( ከድምፃችን ይሰማ የተሰጠ መግለጫ )
ሰኞ ሚያዝያ 12/2007
በአለማችን የተለያዩ ክፍሎች የሰው ፍጡር ክቡርነቱ ረክሶ ፍጡር በፍጡር ላይ ግፍና ጭካኔ የተመላን እኩይ ስራ ሲሰራ ማየት የእለት ተእለት ዜና እየሆነ መጥቷል፡፡ በተለያዩ አካላት፣ መንግስታትም ይሁን ቡድኖች ንፁሀን እንደቅጠል እየረገፉ እናያለን፤ እንሰማለን፡፡ ሰሞኑን እየተሰሙ ያሉት ዜናዎች ደግሞ መላውን ኢትዮጵያዊ እያሳዘኑና አንገት እያስደፉ ይገኛል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች ዜጎች የተሻለ ህይወት ፍለጋ ሀገራቸውን እየለቀቁ ሲሰደዱ ለከፍተኛ አደጋ ይጋለጣሉ። በመንገድ ላይ ዘራፊና ሽፍታ፣ ረሀብና ጥማት፣ እንግልትና እስር ይፈራረቁባቸዋል፡፡ ወደተሻለ ቦታ ለመሻገር ባህር ሲሻገር ሰጥሞ የሚሞተውም ተበራክቷል።
በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎችም አፍሪካውያን ዜጎች ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል እየተፈጸመባቸው ይገኛል። ሰቅጣጩ የጭካኔ ምግባር አፍሪካዊያን ላይ በአፍሪካዊያን የሚፈፀም መሆኑ ደግሞ ይበልጥ አሳዛኝ ያደርገዋል፡፡ ከአስርት ዓመታት በፊት ምእራባዊያን ደቡብ አፍሪካዊያን የሚያደርጉትን የፀረ-አፓርታይድ ትግልና መሪያቸውን ኔልሰን ማንዴላን በ«ሽብርተኝነት» ፈርጀው ሳለም እንኳን ኢትዮጵያና ሌሎች አፍሪካዊያን ትግላቸውን ደግፈዋል፡፡ ይህ ታላቅ ውለታ ተዘንግቶ የተፈፀመው እና ሰሞኑን እያየነው ያለውን የጥላቻና የግፍ ግድያ ሰብአዊ ፍጡር ሁሉ ሊያወግዘው ይገባል። ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችም ይህንን ተግባር በአንድ ድምፅ እናወግዛለን፤ እንቃወማለንም፡፡
በሊቢያም በክርስትያን ወገኖቻችን ላይ አይሲስ በተባለው የሽብር ቡድን የተፈፀመው አሰቃቂ ተግባር ሌላው አሳዛኝ ክስተት ነው፡፡ ይህ ስብስብ የሚሰራውን አሰቃቂ የግፍና የሽብር ተግባር «እስላማዊ» ካባ ሊያላብስ ቢሞክርም በዓለም ዙሪያ ያሉ ሙስሊሞች በአንድ ድምፅ አውግዘውታል፡፡ ጌታችን አላህ በቅዱስ ቁርአን ሱረቱል ማኢዳህ 5፡32 አንድን ነፍስ ያለአግባብ መግደል ሁሉንም ሰብአዊ ፍጡር መግደል እንደሆነ፣ በአንፃሩም አንድን ነፍስ ህያው ማድረግ (መታደግ) ሁሉንም ሰው ህያው እንደማድረግ መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ገልፆዋል። ይህ የሰብአዊ ፍጡርን ሕይወት ዋጋ ትልቅነት የሚያሳይ መሆኑን በርካታ የእስልምና ዑለሞች (ሊቃውንት) ያስረዳሉ፡፡
አይሲስ የተባለው የሽብር ቡድንና «የእሱን ፈለግ እንከተላለን» የሚሉ ሌሎች ቡድኖች ሙስሊሙንም ክርስትያኑንም በግፍ ሲገድሉ ቆይተዋል፡፡ ከህጻናት እስከ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተማሪዎችን በማደሪያ ቦታቸውና በትምህርት ቦታቸው ባሉበት ገድለዋል። ለአምልኮ የተሰባሰቡ ሰዎችን በመስጊድም በቤተ ክርስቲያንም ጨፍጭፈዋል፤ በስደትም ይሁን «በበጎ አድራጎት ተግባር ላይ እንሰማራለን» ብለው ወደሌላ አገር የተጓዙ የሌላ አገር ዜጎችንም ሳይቀር እንደዋዛ በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋል፡፡ ይኸው ትናንት በተሰማ ዜና ደግሞ 28 ኢትዮጵያውያን የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ወንድሞቻችን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ በሽብር ቡድኑ ተገድለዋል። እንደዚህ አይነቱን የሽብር ተግባር በእርግጥም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ከማውገዝም ባሻገር እንደሙስሊምነቱም እንደዜግነቱም አላህ በሰጠው ችሎታ ለመከላከል የበኩሉን ስራ መስራት አለበት፡፡ በተለያዩ ሀገራት በስደት ላይ ሆነው ህይወታቸው ከፍተኛ ችግር ላይ ለወደቁ ዜጎች በተገኘው ቀዳዳ ድጋፍ የመስጠት ስራ ላይ መሳተፍ አስፈላጊ ነው። በግለሰብ፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና ተቋማትም እንዲሁ የሚችሉትን ማድረግ ያስፈልጋል። በመንግስት በኩልም አፋጣኝ ምላሽ ያሻል።
መንግስትም ይሁን ሌሎች አካላት ጊዜው የፖለቲካ ትርፍና ኪሳራ የሚሰላበት፣ አልያም የወቀሳና ክርክር መድረክ የሚፈጠርበት አለመሆኑን ተገንዝበው ዜጎችን የማዳኑ ተግባር ላይ ትርጉም ያለውና ውጤት የሚያመጣ ስራ ላይ መጠመድ ዋነኛ ተግባራቸው ሊሆን ይገባል፡፡ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችም ይህንን ተግባር በይፋ ከማውገዝም ባለፈ በቻልነው ሁሉ ዜጎችን ከአደጋ የመታደግ ስራ ልንሰራ ይገባል። ቤተሰቦቻቸው ለሞቱባቸው ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን!!!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

የብሔር፣ የብሔረሰብ ማንነት ነው የምታጣሩት?

ሰማዕታተ ሊቢያና የሲኖዶሱ መግለጫ
በዲያቆን ዳንኤል ክብረት
የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ አየሁት፡፡ መጀመሪያ ነገር ቋሚ ሲኖዶሱ ተሰብስቦ መክሮበታል ብዬ ለማመን ይቸግረኛል፡፡ 
የተጻፈበት ቋንቋ ቤተ ክህነት ቤተ ክህነት አይልም፡፡ ለመሆኑ ለሰማዕታት የሚሆን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አጥታችሁ ነው? 
ይበልጥ ያስገረመኝ ደግሞ የሰማዕታቱ ዜግነት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ምን እንደሚጠቅማት ነው፡፡ መንግሥት የዜግነትን ጉዳይ ቢያነሣ 
ኃላፊነቱ በዜጎቹ ላይ የተወሰነ ስለሆነ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን ‹መልዕልተ ኩሉ› የተባለቺውን ዘንግታው ነው የዜግነት ጉዳይ 
ያሳሰባት? ምንም ኢትዮጵያዊነታቸው የማያጠራጥር ቢሆንም፣ ጠላታቸው እንኳን የመሰከረላቸው ቢሆንም፣ ዓለም ያወቃቸው 
ቢሆንም፣ ለቤተ ክርስቲያን ግን ሱዳኖችም ሆኑ ሩዋንዳዎች፣ ሶማልያዎችም ሆኑ ጅቡቲዎች የተሠውትኮ ክርስቲያኖች ናችሁ 
ተብለው ነው፡፡ ለአንድ ክርስቲያን የሰማዕትነት ክብሩ የሞተለት ክርስቲያናዊ ምክንያት ነው፡፡ የሞቱት ደግሞ ክርስቲያኖች ናችሁ 
ተብለው ነው፡፡ በቃ፡፡ 
ደግሞስ ‹የዜግነትና የማንነት መረጃውን በተመለከተ ግልጽ መረጃ ለማግኘት ጥረት እየተደረገ ነው› የሚሉን ማነው ጥረት እያደረገ ያለው? መንግሥት ነው ካላችሁ ‹መንግሥት ጥረት እያደረገ ነው› በሉ እናንተም ጥረት እያደረጋችሁ ከሆነ ንገሩን፡፡ 
ቤተሰቦቻቸውኮ ኢትዮጵያ ውስጥ ናቸው፡፡ ለምን ለየሀገረ ስብከቱ መመሪያ በመስጠት ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ከበዳችሁ? 
እረኛ በጎቹን በሪሞት ይጠብቃል እንዴ? 
እጅግ ያስገረመኝና ያሳዘነኝ ነገር ደግሞ ክርስቲያን በመሆናቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደሉ ወንድሞች ከቤተ ክርስቲያን የምጠብቀውን ሦስት ነገር ከመግለጫው ማጣቴ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመታሰቢያ ጸሎት ሊደረግ ይገባው ነበር፡፡ በምንም ለማናውቃቸውና ለማያውቁን የኢንዶኔዥያ ዜጎች ሱናሚ መታቸው ብለን በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ያደረግን ሰዎች ለሚያውቁንና ለምናውቃቸው ክርስቲያን ወገኖች ጸሎት ለማድረግ ለምን እንደከበደን እንጃ፡፡ ለመሆኑ ከአንድ አባት ከጸሎት በላይ ምን ሊገኝ ይገባ ነበር?







‹ማንነታቸው ተረድተን በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት አስፈላጊውን እናድርጋለን› ይላል መግለጫው፡፡ ለመሆኑ ከክርስትና 

በላይ ምን ማንነት አለ? የብሔር፣ የብሔረሰብ ማንነት ነው የምታጣሩት? ከዚያ ይልቅ ሁኔታውን የሚከታተል፣ ከቤተሰቦቻቸው 
ጋር የሚገናኝና ለቀጣዩ የቤተ ክርስቲያን ትውፊታዊም ቀኖናዊም ተግባር ነገሮችን የሚያመቻች ሲኖዶሳዊ ኮሚቴ ይቋቋማል ብዬ 
ጠብቄ ነበር፡፡ ምነው በአንድ አጥቢያ ገንዘብ ተወሰደ ሲባል ሲኖዶሳዊ ኮሚቴ ይቋቋም የለምን? 

ሦስተኛው ያሳዘነኝ ነገር ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ላይ የሚደርሰውን ኀዘን የምትገልጥበት ቀኖናዊና ትውፊታዊ ሥነ ሥርዓት የሌላት 

ይመስል ኀዘንን በሴኩላር መንገድ ስትገልጥ ማየቴ ነው፡፡ እኔ የጠበቅኩት ለአንዳንድ ክርስቲያን ላልሆኑ ‹ታላላቅ ሰዎች› ቀብር 
እንኳን የሚከፈተው የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከፍቶ፣ ለቢዮንሴ እንኳን ያልተነፈጋት ማኅሌት ተቁሞ፣ በፓትርያርኩ የሚመራ 
ጳጳሳቱ የሚገኙበት የጸሎት ሥነ ሥርዓት ተደርጎ፣ መግለጫው በጸሎቱ ፍጻሜ ይሰጣል ብዬ ነበር፡፡ የመግለጫው አሰጣጥ ግን 
የዕለት ተዕለት ተግባርን በተመለከተ የሚሰጥ ሳምንታዊ መግለጫ ነበር የሚመስለው፡፡ ኦርቶዶክስ ኦርቶዶክስ አይሸትም፡፡ 
የተወካዮች ምክር ቤት እንኳን የሦስት ቀን ብሔራዊ ኀዘን ሊያውጅ መሆኑን ሲገልጥ ቤተ ክርስቲያኒቱ ግን የጸሎት ሳምንት 
አለማወጇ የታሪክ ትዝብት ውስጥ የሚከታት ነው፡፡ 

እኔ የሲኖዶሱ መግለጫና አገላለጡ ወርዶብኛል፡፡ ሲኖዶሳዊም መስሎ አልታየኝም፡፡ ሊቃውንቱ ያዩት፣ ጳጳሳቱ የተወያዩበት፣ 

ቅዱሳት መጻሕፍቱ ያሹት፣ ቀኖናዎቹ የዳሰሱት፣ ትውፊቱ የነካው፣ ባሕሉ ያጠነው አልመስልህ አለኝ፡፡ ‹ወይ እንደ 
እስክንድር ተዋጋ ወይ የእስክንድርን ስም መልስ› አለ ታላቁ እስክንድር፡፡

Sunday 19 April 2015

ISIS በመባል የሚጠራው የአረመኔዎች ጥርቅም 28 ኢትዮጵያውያንን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ ገደለ

  የእስላም አክራሪ ድርጅት የሆነው ISIS በመባል የሚጠራው  የአረመኔዎች ጥርቅም  28 ኢትዮጵያውያን ን በሊቢያ  በአሰቃቂ ሁኔታ ገደለ ᎓᎓ 

ዛሬ አልጄዚራ እነደዘገበው የ12ቱ አንገት በባህር ዳርቻው በካራ ሲቀላ የ16ቱ ጭንቅላት ደግሞ በበረሀው መሀል በጥይት ተነድሏል። 

በስደት አለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰው ኢ ሰብዓዊ ግፍ እና ግድያ ከዕለት ወደ እለት ከመቼውም ግዜ 

እየጨመረ መጥቶአል ᎓᎓ በአረብ ሃገራት  በሳውዲ ፣ በየመን ፣ በቤሩት ፣ እና በሌሎች ሃገራት እንዲሁም በአፍሪካ በኬንያ ፣ 

በሱዳን ፣ በደቡብ አፍሪካ ፣ በሊቢያና በሌሎችም የአረብና የአፍሪካ ሃገሮች ኢትዮጵያውያን በተሰደዱበት ሃገራት እየተገደሉ 

እየታፈኑና በየእስር ቤቱ እየተንገላቱ ሰብዓዊ ክብራቸው ተጥሶ  በሞትና በስቃይ ላይ ይገኟሉ ᎓᎓ 



ኢትዮጵዊ በዚህ መልኩ በአለም ፊት  ሲዋረድና  ሲገደል  እኛ ኢትዮጵያውን ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ዝም ብለን ማለፍ የሚገባን ነገር አይደለም ᎓᎓ ኢትዮጵያ መንግስ አልባ ሃገር መሆናን በሚገባ እየተመለከትን  እንገኟለን ᎓᎓ ህዝባችን የችግሩ መፍትሄ በእጁ ነው ያለው በስደት ያተረፍነው መከራና ሞት ነው ᎓᎓ በስደት አገር እንዲህ ሆኖ ከመሞት  ለአገራችን በሚደረገው ለፍትህ ለነፃነት ለእኩልነት  ትግል በመሳተፍ መሞት የበለጠ ክብር ነው ᎓᎓ ለአገራችን ህልውና እና ለህዝባችን  ክብር ዘላቂ መፍትሄው በጋራ በመቆም ለዚህ ያበቃንን ችግር በመተባበር በማስወገድ ዘለቄታ ያለው  የችግራችንን መፍትሄ አሁኑኑ  ከተግባር ጋር መወሰን ይኖርብናል ᎓᎓

በግፍ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያንን  ነፍስ በገነት ያኑርልን !

እነዚህን ሊንኮች በመክፈት መመልከት ይችላሉ᎓᎓

http://www.aljazeera.com/news/middleeast/2015/04/isil-claims-massacre-ethiopian-christians-libya-150419104309814.html

ቪዲዮ http://www.vocativ.com/world/isis-2/isis-video-shows-mass-beheading-of-ethiopian-christians-in-libya/?fb_action_ids=848501618548970&fb_action_types=og.shares
http://www.jpost.com/Middle-East/New-Islamic-State-video-shows-shooting-beheading-of-Ethiopian-Christians-398563


በደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያኖች ላይ የሚደርሰውን ጭካኔያዊ ግድያ

ሮዚና አለም ተስፈዬ የተባለች አትዮጵያዊት ከደርባን በሜሴንጀር በላከችልኝ መልዕክት መሠረት እነዚህ በአንገታቸው ላይ ጎማ የተጠለቀባቸው ሦሥት ወጣቶች ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡የሮዚና መረጃ ትክክል ከሆነ የዛሬ ሳምንት በሱቃቸው እያሉ የእሳት ጥቃት የተፈፀመባቸውን ሁለቱን ኢትዮጵያውያን ስንጨምር ቁ ጥሩ ወደ 5 ከፍ ይላል፡፡ከነዚህ ውስጥ አነዚህ ሶስቱና ሳምንት ከተጠቁት ሁለቱ አንዱ ስለሞተ የሟቾች ቁጥር 4 ነው፡፡
በፅኑ የቆሰለው አንደኛው ሆስፒታል ሕክምና ላይነው፡፡ ትናንት ተጠልፈው የተወሰዱና ይሙቱ ይዳኑ ያልታወቁ ሶስት የጠፉ ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡ይህ ብቻ እንኳ የአትዮጵያንን ቀጥተኛ ጥቃት ወደ 8 ያደርሰዋል፡፡በዐለም አቀፍ ሚዲያ የሚገለጸው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ትናንት በሲኤን ኤን ዘገባ ድንበር ላይ ያነደዱትን ዚምባብዌያዊ አይቻለሁ፡፡ሌላ አንድ ሞተረኛን፣አንድ ደግሞ እላዩ ላይ እሳት ጭረውበት የሚያደርገው ጠፍቶት እንደ እብድ ወዳገኘበት ሲሮጥና ተከታትለው በጠረባ በመጣል ጎማ በአንገቱ አስገብተው ሲያነዱት አይቻለው፡፡እሱ የነደደበት ቦታ ላይ ነው ሞተረኛውን ከነሞተሩ የጣሉትና ያጋዩት፡፡እዛው የነበረና ቀይ ሹራብ የለበሰ ወጣት ድንገት ተናነቁት፡፡
አምልጬ እሔዳለሁ ሲል አንዱ በጣውላ አናቱ ላይ መታው ፤እነሳለው ሲል አንዱ ፊቱን ረገጠው፤ሌላው በጣውላው ደገመው ፡፡ከዛ እሳቱ ውስጥ ማገዱት፡፡ብዙ ደቂቃ እንደእንጨት ሲቃጠሉ በሕይወት ነበሩ፡፡

ሌሎች ዕድሜያቸው ከ14 21 ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ወጣቶች ሢቃጠሉ አይቻለሁ፡፡ሌሎች ሁለት እንደ አይጥ አሰፈልት መሐል በድንጋይ ተጨፍልቀው ፣በአጠና ተጨጭፈውና በእግር ተረጋግጠው ሢሞቱ አይቻለሁ፡፡አለም አቀፍ ሚዲያዎች የሚሠጡን ቁጥሮ ግን አስቂኝ ነው፡፡እስካሁን አምስት ሰዎች ተገደሉ ይሉናል፡፡በቂ መረጃ እያገኘን አይደለም፡
አለምነህ ዋሴ


Monday 13 April 2015

BEYOND THE POLITICS OF THE NILE

BEYOND THE POLITICS OF THE NILE – ANALYSIS – By Minga Negash, Seid Hassan, Mammo Muchie and Abu Girma

Nile-River


ANALYSIS, EGYPT, ENVIRONMENT, ETHIOPIA, SUDAN
By Minga Negash, Seid Hassan, Mammo Muchie and Abu Girma*

On March 23, 2015, Egypt, Ethiopia and the Sudan signed a declaration of principles on the Grand Ethiopian Renaissance Dam[1] (GERD). Since then, an intense debate has been going on regarding the modalities and core principles which were spelled out in the Declaration. Unfortunately, the principles contained in the Declaration have invited unhealthy rhetoric, particularly within Egypt, Ethiopia and among the Ethiopian diaspora.
There are two fundamental reasons for the negative discourses. The first one involves the non-cooperative, zero-sum game strategic behavior that is inherent within the actions of the parties. Game theorists, political scientists and economists very well know that shared watercourses invite unilateral and self-interest maximizing actions – the well-known zero-sum positions being the dominant solution. Added to this is the emotive nature of the Nile River that was instigated and imposed upon the peoples of the region by colonialism. The second has to do with Egypt’s long-held historical ambitions to control the sources of Nile and colonial era position that is still reflected in the Declaration. On closer examination, we find that several of the current stipulations of the Declaration include many of the key elements of the 1929 and 1959 “Nile Water Agreements” that Ethiopia was not a part to. Consequently, the Declaration is framed not in a positive-sum game- “win-win” manner.
Cognizant of the fact that the construction of the Grand Renaissance Dam has become a game changer, with its strong potential to lead to cooperation, we attempted to show that Egypt’s policy towards Ethiopia has been unsustainable. We did so in our April 30, 2014 commentary. Even though we did not have the full and official Declaration in hand at the time of writing, we also attempted to raise awareness as well as our concerns using a short commentary that we disseminated on 23 March, 2015. In particular, we called for (i) the translation of the actual Agreement into various Ethiopian languages; (ii) the revision of certain clauses; and (iii) as Egypt’s President was heading to address the Ethiopian Parliament and request for ratification, we called upon the Government of Ethiopia to defer this process to allow time and space for reflection. After the release of that commentary, Aiigaforum.com[2] , a website that is close to the Government of Ethiopia, posted a document which purports to be the final and authentic version of the Agreement. Except for the location of the signing, and singular-plural uses of certain terms, see for example “resources” versus “resource” in the preamble, and the sequence of the numbering of Principles III and IV of the Agreement, when compared to other versions available on the internet, the document appears to be authentic.[3] Though speculations are rife that the final agreement is still a secret, because of the importance of the matter, for this commentary we have used the version that was made available by Aigaforum.com.
Many have opined and welcomed the recent Egyptian diplomatic overture towards Ethiopia, and its acceptance of the construction of the GERD, in particular. Even though the current tripartite Agreement seemed to have temporarily eased the recent tension among the parties, and despite some of the positive aspects of the Egyptian diplomatic overtures and its intent to cooperate as spelled out in the Declaration, we observe that the Agreement is unsustainable in its current form.
In fact, our examination of the Declaration of principles leads to the conclusion that the clauses are designed to re-assert the 1929 and 1959 water sharing agreements and the much criticized Framework for General Co-operation Between the Arab Republic of Egypt and Ethiopia, July 1993, Cairo, Egypt[4] that was signed by the then Presidents of Egypt and Ethiopia. In this follow up commentary on GERD, we independently examine, in a non-technical manner, the elements of the tripartite Agreement which was signed in Khartoum on March 23.
We do so by identifying omissions, sticky points and mistakes that need attention. Consistent with our April 30, 2014 commentary on this topic, we attempt to decouple political posturing within Ethiopia from the trans-boundary water issues that are facing the country. In doing so, we focus on the substantive issues so that the country avoids the repeat of the mistakes in the Algiers Agreement of 2000 between Eritrea and Ethiopia and the series of diplomatic maneuvering that created a landlocked country in 1993.[5] We decided to incorporate the clauses that are contained in the Declaration for the reader’s convenience.

ANALYSIS OF THE AGREEMENT

There are ten principles stated in the current Agreement. Below we provide comments for each element in the Agreement. For convenience, we juxtapose the Agreement (as published in www.aigaforum.com) and our comments follow the article. Concluding remarks are provided in section III.

I. PRINCIPLE OF COOPERATION

  • To cooperate based on common understanding, mutual benefit, good faith, win-win, and principles of international law;
  • To cooperate in understanding upstream and downstream water needs in its various aspects.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) This article is not very different in spirit from the framework for cooperation that was signed between Egypt and Ethiopia in 1993. The intent of this principle appears to invoke clauses in the UN’s Convention on the Law of the Non-Navigational Uses of International Watercourses that was adopted on 21, May, 1997[6] and the Declaration on Principles of International Law Concerning Friendly Relations and Co-operation among States in accordance with the Charter of the United Nations, G.A. res. 2625, Annex, 25 UN GAOR, Supp. (No. 28), U.N. Doc. A/5217 at 121 (1970). It is however important to note that 17 years after its adoption, other than the United Kingdom no major power has signed the non-navigational use of international waters Convention. By the end of 2014, only 38 countries (out of about 194 Member States) have signed/accepted and ratified it[7] . It is also interesting to note that 11 of the 38 countries are located in the African continent. None of the three countries (Egypt, Ethiopia and Sudan) have signed, accepted or ratified this Convention.
(2) The most controversial element of the 1997 UN Convention is Article 7 which deals with “not to cause significant harm” by upstream countries on downstream countries. Concerned by the ramifications of this clause, many upstream countries that have important trans-boundary rivers are either shying away from ratifying the Convention or are openly objecting to it as the Convention: (i) does not provide for compensation to upstream countries for lost opportunities, and (ii) exposes them to an indeterminate and uninsurable risk. As we shall see below, Article 7 features in both the recently signed tripartite Agreement (without recognition of opportunity costs and damage limitation clause) and in Article 5 of the 1993 agreement between Egypt and Ethiopia.
(3) The Phrase “principles of international law” neither implicitly nor explicitly recognizes the existence of Nile Basin Cooperative Framework Agreement. Hence it fails to guide a comprehensive agreement pertinent to the region.[8]
(4) The phrase “in its various aspects” suggests that downstream countries need additional waters or if they decide to develop new habitations, the upstream countries may have to give up their development opportunities. Research shows that downstream countries are usually densely populated and industrialized, have flatter topographies and hence their water needs are higher than upstream countries. Furthermore, even though the Agreement is about the GERD (see the heading and the preamble of the Agreement), the Article is sweeping and covers the entire river system as we shall see below.

II. PRINCIPLE OF DEVELOPMENT, REGIONAL INTEGRATION AND SUSTAINABILITY

• The purpose of GERD is for power generation, to contribute to economic development, promotion of trans-boundary cooperation and regional integration through generation of sustainable and reliable clean energy supply.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

The text states that the purpose of the project is to generate “sustainable and reliable clean energy supply”. There are no auxiliary purposes and can be interpreted to exclude, for example, the use of the waters for fishing, recreation, education and small scale industrial and irrigation projects around the dam. We do think that there are costs (risks) in agreeing to this clause by the upstream country. There are no provisions for planting trees (timber, coffee, etc.), for example, to mitigate the erosion and evaporation, capture the carbon and/or put the soil into better use. This clause is, therefore, devoid of shared benefits and responsibilities.

PRINCIPLE EQUITABLE AND REASONABLE UTILIZATION

  • The three countries shall utilize their shared water resources in their respective territories in an equitable and reasonable manner
  • In ensuring their equitable and reasonable utilization, the three countries will take into account all the relevant guiding factors listed below, but not limited to the following outlined:
a) Geographic, hydrographic, hydrological, climatic, ecological and other factors of a natural character;
b) The social and economic needs of the Basin States concerned;
c) The population dependent on the water resources in each Basin State;
d) The effects of the use or uses of the water resources in one Basin State on other Basin States;
e. Existing and potential uses of the water resources;
f) Conservation, protection, development and economy of use of the water resources and the costs of measures taken to that effect;
g) The availability of alternatives, of comparable value, to a particular planned or existing use;

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) Even though this principle appears to be normal, it obligates Ethiopia to continue honoring Article 5 of the 1993 cooperation framework between Egypt and Ethiopia.
(2) Sub-article III (e), which deals with the existing and potential uses of the water resources, is a sticky point. It shall continue to be a source of tension as it is the focal point of the relationship between upstream and downstream countries. It needs to be examined in the light of the principles that are enshrined in the Nile basin framework.
(3) Sub-article III(f) does not sufficiently obligate downstream countries to invest in water conservation and rationalization. The laxity in this sub-article legitimizes the increased demand for water by downstream countries.
(4) The scope of the Agreement does not include ground water resources available in downstream countries.

PRINCIPLE OF NOT TO CAUSE SIGNIFICANT HARM

  • The Three Countries shall take all appropriate measures to prevent the causing of significant harm in utilizing the Blue/Main Nile.
  • Where significant harm nevertheless is caused to one of the countries, the state whose use causes such harm shall, in the absence of agreement to such use, take all appropriate measures in consultations with the affected state to eliminate or mitigate such harm and, where appropriate, to discuss the question of compensation.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

As indicated above, this clause is taken from Article 7 of the 1997 UN Convention on the Law of the Non-navigational Uses of International Watercourses 1997- (effective as of April, 2014). The “obligation not to cause significant harm” is related to the age-old economic theory of externality which features in European trans-boundary waters and environmental agreements, in the form of the “polluter pays principle”. The UN Convention states that:
“(a) Watercourse States shall, in utilizing an international watercourse in their territories, take all appropriate measures to prevent the causing of significant harm to other watercourse States.
(b) Where significant harm nevertheless is caused to another watercourse State, the States whose use causes such harm shall, in the absence of agreement to such use, take all appropriate measures, having due regard for the provisions of articles 5 and 6, in consultation with the affected State, to eliminate or mitigate such harm and, where appropriate, to discuss the question of compensation.”
Article #2 of the 1997 Convention defines the term “watercourse” as follows:-
“Watercourse” means a system of surface waters and ground waters constituting by virtue of their physical relationship a unitary whole and normally flowing into a common terminus.”
It is interesting to note that the tripartite Agreement avoids the use of the term “watercourse” and hence excludes the ground water resources in Egypt and Sudan that recent geoscience studies are indicating.[9] Furthermore, it is important to note that the “international law” is selectively used here to strengthen the position of the initiator-originator of the current text.
(1) The opening paragraph of the tripartite Agreement starts with a rather misleading sentence. It states that “the three countries shall take all appropriate measures….” The article specifically deals with damages and not “causing significant harm in utilizing the Blue/Main Nile”. The Blue/Main Nile originates from the highlands of Ethiopia and contributes approximately about 85 percent of the water to the Nile River system, and hence this clause is about Ethiopia.
Downstream countries are not affected by this clause as Ethiopia is. The clause is unambiguous in giving downstream countries right to “take appropriate measures to prevent significant damage” by the upstream country. The obvious issue that emerges here is sovereignty over the waters of the Blue/Main Nile, and the issue is more than likely to be a sticky point in that neither sovereign equality nor territorial integrity clauses (see Principle # IX below) are sufficient to protect Ethiopia. In fact there is concern that it can be construed as a voluntary ceding of sovereignty by Ethiopia.
(2) The phrase “significant harm is not defined” and there are no thresholds about water sharing, physical damages arising from faulty construction/management of the dam and Act of God. Hence it is subject to various interpretations.
(3) The clause refers to the Blue Nile/Main River. The Blue Nile/Main River has tributaries. In the absence of an exclusion clause for the tributaries, the clause maybe used to restrict Ethiopia from developing irrigation projects on any of the tributaries of Blue Nile.

PRINCIPLE TO COOPERATE ON THE FIRST FILLING AND OPERATION OF THE DAM

  • To implement the recommendations of the International Panel of Experts (IPoE), respect the final outcomes of the Technical National Committee (TNC) Final Report on the joint studies recommended in the IPoE Final Report throughout the different phases of the project.
  • The three countries, in the spirit of cooperation, will utilize the final outcomes of the joint studies, to be conducted as per the recommendations of the IPoE Report and agreed upon by the TNC, to:
a) Agree on guidelines and rules on the first filling of GERD which shall cover all different scenarios, in parallel with the construction of GERD.
b) Agree on guidelines and rules for the annual operation of GERD, which the owner of the dam may adjust from time to time.
c) Inform the downstream countries of any unforeseen or urgent circumstances requiring adjustments in the operation of GERD.
d) To sustain cooperation and coordination on the annual operation of GERD with downstream reservoirs, the three countries, through the line ministries responsible for water, shall set up an appropriate coordination mechanism among them.
e) The time line for conducting the above mentioned process shall be 15 months from the inception of the two studies recommended by the IPoE.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) Implicit in Article V is that the project is going ahead. Only the filling of the reservoir and operational/functional matters of the dam are to be negotiated. The presumption is that the pace of the filling should be slow enough to supply water to downstream countries but fast enough to satisfy Ethiopia’s needs as the NPR’s reporter has put it.
(2) This article however crucially depends on a report that is yet to be produced. Theleaked IPoE report vindicates Ethiopia on many fronts and as we indicated in our April 30, 2014 commentary the deficiencies are not insurmountable. It remains to be seen whether the TNC report will be different from the one produced by IPoE. Notwithstanding this, the environmental aspect of the TNC report is expected to echo Egyptian concerns. It is important that the environmental impact assessment of the project be comprehensive and linked to (i) current and potential ground water resources in downstream countries and (ii) the rather wasteful use of the resource in downstream countries and pollution around the delta.
(3) Sub-article V(b) refers to the “owner” of the dam, in the singular, and resolves the speculation about joint ownership, at least for the moment. As a result of the sensitivity of the project, we encourage the Government of Ethiopia not to allow either equity or linked participation at this time.[10]

PRINCIPLE OF CONFIDENCE BUILDING

  • Priority will be given to downstream countries to purchase power generated from GERD.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) Clean energy production and sale reduces the downstream countries’ dependency on fossil fuel generated energy. Hence, this is not just a “confidence building” issue. It has direct and measurable economic consequences, and hence needs to be imputed in the pricing of electricity for the proposed sale.
(2) In many economies electricity falls within rate regulated industries. Hence, pricing for domestic use will be different from pricing for export. International pricing will be a more complicated issue and may not be easily decoupled from the type of intergovernmental relationships that emerge in the region.
(3) The word “will” is equivocal since it has several meanings in the legal lexicon as in thesaurus, and hence may serve as a point of future contention.

PRINCIPLE OF EXCHANGE OF INFORMATION AND DATA

• Egypt, Ethiopia, and Sudan shall provide data and information needed for the conduct of the TNC joint studies in good faith and in a timely manner.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) As indicated earlier, the IPoE had already stated that the social and environmental aspects of the project in downstream countries need an additional study. The availability of such information should enable Ethiopia to complete the study. As indicated above, the study however needs to be comprehensive, and does not have to be confined to the project.
(2) Data accuracy, completeness and integrity can be sticky problems.
(3) Certain technical (engineering design, formulae, etc.) information might be proprietary and therefore confidential. The parties need to determine the minimum level of disclosure.

PRINCIPLE OF DAM SAFETY

  • The three countries appreciate the efforts undertaken thus far by Ethiopia in implementing the IPoE recommendations pertinent to the GERD safety.
  • Ethiopia shall in good faith continue the full implementation of the Dam safety recommendations as per the IPoE report.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) Dam safety is as important for Ethiopia as it is for downstream countries. Notwithstanding this it is important to ensure that “best practice” is followed so that habitations and civilizations in downstream countries are not threatened by faulty construction and substandard operations.
(2) Downstream countries are formally acknowledging Ethiopia’s compliance effort, and it is good.

PRINCIPLE OF SOVEREIGNTY AND TERRITORIAL INTEGRITY

  • The three countries shall cooperate on the basis of sovereign equality, territorial integrity, mutual benefit and good faith in order to attain optimal utilization and adequate protection of the River.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

(1) The concept of “sovereign equality” features in many international agreements, conventions and constitutive acts (example the African Union), and is defined in the UN 1990’s Declaration on Principles.[11] It states that “sovereign equality” includes the following elements: (a) States are judicially equal; (b) Each State enjoys the rights inherent in full sovereignty; (c) Each State has the duty to respect the personality of other States; (d) The territorial integrity and political independence of the State are inviolable; (e) Each State has the right freely to choose and develop its political, social, economic and cultural systems; (f) Each State has the duty to comply fully and in good faith with its international obligations and to live in peace with other States.[12]
(2) This article is fairly standard and also features in the 1993 framework. However, it is unlikely to override the articles the dealt with damages and rights that appear to have been voluntarily ceded to downstream countries in connection with the Blue/Main Nile and its tributaries.

PRINCIPLE OF PEACEFUL SETTLEMENT OF DISPUTES

  • The Three countries will settle disputes, arising out of the interpretation or implementation of this agreement, amicably through consultation or negotiation in accordance with the principle of good faith. If the Parties are unable to resolve the dispute through consultation or negotiation, they may jointly request for conciliation, mediation or refer the matter for the consideration of the Heads of State.

OUR BRIEF ASSESSMENTS

This article is also fairly standard. It evolves from the UN 1990 Convention and that of the UN Charter. When this article is read together with Principle 1 of this tripartite Agreement, it brings back the 1997 Convention and the mediation, arbitration and determination role of the International Court of Justice. Ethiopia’s experience with arbitration has not been good and the Algiers Agreement and the ruling made by the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission[13] are too fresh to be forgotten. Despite this fact, with lopsided clauses stacked against Ethiopia and in the absence of sound rules and principles governing the Nile water allocation and management, a “third party”, particularly in the context of the Nile Basin Cooperation Framework Agreement may lead to a better outcome.

CONCLUDING REMARKS

In summary, when the recent tripartite Agreement on the GERD is compared with the 1993 bilateral agreement, though in many respects the spirits of the two agreements appear similar, there are also important differences. The current Agreement reaffirms Article 5 of the 1993 agreement which favored Egypt, includes terms about compensation for damages, restricts the scope of the dam project, recognizes “rights” to take action on the Blue/Main Nile, is sloppy on water utilization in downstream countries, and the non-exclusion of the tributaries from the Agreement cumulatively puts Ethiopia at a disadvantage.
The obvious and fundamental question that arises in the minds of many observers is whether a reasonable government representative of an independent upstream country, irrespective of his/her political credo, would sign without duress, the tripartite Agreement in its present form. In light of the above analysis and consistent with our initial reaction of March 24, 2015, we reiterate our statement that no free nation should be subjected to be a party to such a lopsided and risky Agreement.
We also think the shared Nile waters represent opportunities for all riparian counties. However, the good fortunes emanating from the Nile could only be leveraged if all riparian countries are able to overcome the seemingly self-interest maximizing but counter-productive zero-sum game actions. The Nile Basin can facilitate the much needed African regional integration if all parties know how to share both the cost and benefit from this rich resource. Hence, the central point of departure for making bilateral, tripartite, quadripartite (as the case may be) agreements should be the Nile Basin Cooperative Framework Agreement, which includes all the riparian states and centers around the equitable sharing of the trans-boundary watercourses. Egypt must not be allowed to divide and maintain its supremacy by undermining the regional cooperation framework that is already in motion.
Hence, in the interest of equitable, fair, sustainable, comprehensive solution that guarantees shared benefits and responsibilities, we, therefore, call upon:
  • Policymakers and stakeholders of all ripari counties to understand that trans-boundary water flows, by their nature, are susceptible to the tragedy of the commons- that attempts by individual nations acting independently or in a dominant manner could only damage the common resource, and recognize that only shared responsibilities could guarantee shared benefits;
  • The parties to the current Declaration rectify the unfair, unequitable and unsustainable clauses that are damaging to any party, Ethiopia, in particular;
  • All political parties in the riparian states refrain from using the shared waters of the Nile for their self-preserving interests;
  • The Declaration and future negotiations should evolve from the laudable Nile Basin Cooperative Agreement;[14]
  • Any signed treaties and declaration of principles be immediately translated into major Ethiopian and other riparian states languages so that the general public is aware of what is going on;
  • Hydrologists, economists, lawyers, ecologists, geoscientists, sociologists, water engineers and diplomats etc., in the region to make professional contributions so that the water sharing problem is resolved for the benefits of all in the region.
*About the authors:
Minga Negash, Professor of Accounting at MSU Denver (U.S.A) and the University of the Witwatersrand (South Africa)

Seid Hassan, Professor of Economics at Murray State University (U.S.A)
Mammo Muchie, Professor of African Innovations at Tshwane University of Technology (South Africa), Visiting Professor, Shanghai University (China)
Abu Girma, TMDC, Oxford University
Notes
[8]See for example 
[10] “Declaration on Principles of International Law Concerning Friendly Relations and Co-operation among States in accordance with the Charter of the United Nations, G.A. res. 2625, Annex, 25 UN GAOR, Supp. (No. 28), U.N. Doc. A/5217 at 121 (1970)”.


ድሆች በዚች አገር መጠጊያና መውደቂያ የላቸውም ማለት ነው ?

ሪፖርተር 
መንግሥት የኮዶሚኒየም ቤቶችን ፕሮጀክት እውን ያደረገበት ዋነኛ ምክንያት በቤት ችግር ምክንያት የሚሰቃየውን የአዲስ አበባ ኗሪ፣ በተለይም ደግሞ ድሆችን የቤት ባለቤት ለማድረግ እንደሆነ ተደጋግሞ ሲገለጽ ሰምተናል፡፡
አሁንም መንግሥት ይህንኑ የጀመረውን ቤት አልባ ኗሪዎችን የቤት ባለቤት የማድረግ ራዕዩን ሙሉ በሙሉ የተሳካ ለማድረግ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ወጪ በማድረግ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡
ይህ ሁላችንም እንደ ዜጋ ይበል የሚያሰኝና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቃሉን በተግባር የመጠበቅ አካሄድ ስለሆነ ደስ የሚያሰኘን ነው፡፡ ይሁን እንጂ አስተዳደሩ ቤት አልባ የአዲስ አበባ ኗሪዎችን ባለቤት አደርጋለሁ ባለው ቃሉ ተጠቃሚ እየሆኑ ያሉት በአብዛኛው አቅም ያላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ኗሪዎች እንደሆኑ ግን በግልጽ እያየን ነው፡፡ ድሆች ዛሬም የዜና ማድመቂያ እንጂ የዕድሉ ተጠቃሚ መሆን አልቻሉም፡፡
ከሁለት ዓመታት በፊት አስተዳደሩ በነደፈው ዕቅድ መሠረት የከተማውን ኗሪዎች እንደየአቅማቸው የቤት ባለቤት ለማድረግ በነበረው ምዝገባ ወቅት ዓይኖቻችን ብዙ ጉድ አይተዋል፡፡ ውኃ የመሰለ መኪናቸውን ያቆሙ፣ በውድ አልባሳትና ጌጣጌጦች ያሸበረቁ ሰዎች ከእኛ ከድሆቹ እኩል እየተጋፉ ሲመዘገቡ ታዝበን በእውነት እነዚህ ሰዎች አንድ አይደለም ሁሉት ሦስት ቤት የላቸውምን? ስንል የሆዳችንን በሆዳችን አድርገን ብንናገርስ ድሃን ማን ሊሰማው በማለት አርፈንና አፍረን ተቀምጠን ነበር፡፡
እነዚሁ በውጭ አገር የሚኖሩ ልጆቻቸውንና ቤተሰባቸውን የቤት ባለቤት ለማድረግ እኛ ሙሉውንም ቢሆን መክፈል እንችላለን በማለት በእኛ በድሆቹ ላይ ሲመጻደቁ፣ የድሆች አምላክ ፈጣሪ አንተ ሁነና ብለን ወደ ላይ ተማጽነናል፡፡ መንግሥት በኪራይ እየተሰቃዩ ያሉ የከተማችንን ኗሪዎች በተለይም ደግሞ ድሆችን ተጠቃሚ እናደርጋለን በማለት ምሎ ቢገዘትም፣ የቤት ባለቤት የሆኑ ሰዎች የደረሳቸውን የኮንዶሚኒየም ቤቶች ለሌላ ሦስተኛ ወገን በማከራየት እየተጠቀሙ ያሉ በርካታ ሰዎች እንዳሉ ግን የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡
እንዲህ የገንዘብ አቅም ያላቸው ሰዎች ድምፅ ብቻ በሚሰማባት አገር ውስጥ ከአሥር ዓመታት በላይ ተመዝግበው ከነገ ዛሬ ቤት ይደርሰናል ብለው በጉጉት ሲጠባበቁ የነበሩና በድኅነት ተቆራምደን ያሳደግናቸውና የነገ ተስፋ ይሆኑናል ብለን ያልናቸው ልጆቻችን፣ በተከታታይ ገንዘብ አልቆጠባችሁም በሚል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዕጣ ውጪ በማድረግ ለእኛም ለልጆቻችንም አንጀታችንን የሚበጥስ ወሬ አሰማን፡፡
ለመሆኑ ይህች አገር ድንበሯ ሲጣስ፣ በጠላት ስትወረር ለነፍሱ ሳይሳሳ፣ ዛሬ ተደላድላችሁ የምትመሯትን አገር ደሙን አፍስሶ አጥንቱን ከስክሶ ያቆየው የትኛው ኅብረተሰብ ክፍል ነው፣ ድሃው አይደል እንዴ?! አቅም ያላቸውና ባለገንዘቦቹማ አገር በጭንቅ ስትያዝ በባሌም ሆነ በቦሌ ብለው የአገራቸውን ጭንቀትና ብሶት ወደማያዩበትና ወደማይሰሙበት ወደ አውሮፓና አሜሪካ አይደል እንዴ የሚሰደዱት?
ይኸው ድሃ ሕዝብ አይደል እንዴ በውድም ሆነ በግድ ሠልፍ ውጣ ሲባል ሠልፍ ወጥቶ፣ ተነስ፣ ዝመት፣ ሲባል እሺ ብሎ አንገቱን ደፍቶ የሚታዘዛችሁ? ሠልፋችሁንም ሆነ በዓላችሁን የሚያደምቀው ለመሆኑ የትኛው ሕዝብ ነው፡፡ ታዲያ ይህን የሁልጊዜም ባለውለታችሁ የሆነውን ድሃ ሕዝባችሁን በአገሩ፣ በገዛ ምድሩ ላይ አንዲት ነፍሱን የሚያስጠጋበት መጠለያ እንዳይኖረው ማድረግ የግፍ ግፍ አይደለም እንዴ?!
እነዚህ በድኅነት ተምረው አሁንም ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ገቢ እኛን ቤተሰቦቻቸውን እየደጎሙ ያሉ ልጆቻችን ከየትኛው ደመወዛቸው ተርፎአቸው ነው እናንተ እንደምትሉት በየወሩ 200 እና 300 ብሮችን መቆጠብ የሚችሉት? በተከታታይ ለመቆጠብ አቅሙ ያነሳቸው ልጆቻችን ዕጣ ውስጥ ተካተው ቤቱ ቢደርሳቸው ኖሮ እኛ ወላጆቻቸውም ሆንን እነርሱ ከየትም ከየትም ብለን፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንም ለምነን ቢሆን የዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንችል ነበር፡፡ መቼም ሕዝባችን አይጨክንብንምና!!
ግና እኛም ሆነ ልጆቻችን አሁን ምን ዕድል አለን? መንግሥት ድሆች በዚህች ምድር ላይ ቦታም ዕድልም የላቸውም በማለት እንደ አሮጌ ቁና ገፋን፡፡ ለዚህች ምድር ነፃነትና ልዑላዊነት ደማችን እንዳልፈሰሰ፣ ድሆች ልጆቻችን ከእናታቸው ጉያ እየተነጠቁ በደስታውም በሐዘኗም ወቅት ለአገራቸው በግንባር ቀደምትነት ራሳቸውን አሳልፈው እንዳልሰጡ፣ ዛሬ ነፍሳቸውን የሚያስጠጉበት መኖሪያ ተነፈጋቸው፡፡ ለድሆች ቁሜያለሁ የሚለው መንግሥታችንም አቅም ለሌላቸው የከተማችን ኗሪዎች፣ መናጢ ድሆች የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ነገር ወደፊት እናመቻቻለን ሲል ተሳለቀብን፡፡
‹‹እኔ የምሞተው ዛሬ ማታ እህል የሚደርሰው ለፍልሰታ›› እንዲሉ አበው በዚህች አገር እኛ ድሆች በሞት አፋፍ ላይ ስንሆን ነው ማለት ነው የሚታሰብልን፣ መጠጊያና መድረሻ የሌለን እኛ ድሆችስ በዚህች አገር የውራ ውራ የሆንን ዜጎች ነን ማለት ነው?! እኛ ድሆች፣ ልጆቻችንና ቤተሰባችን መቼም አላማረባችሁምና በሚል እንዲህ እንደተንከራተቱ ይኑሩ ብላችሁ ጨክናችሁ ከፈረዳችሁብን እንግዲህ ምን እንላለን? የድሆች አምላክ፣ የኢትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ይፍረደን ከማለት ውጪ፡፡ አምላክ አገራችንን በሰላም ይጠብቅልን፣ ሕዝባችንንም ከስደትና ከመከራ ይሰውርልን!!
(አያ ምሕረቱና ቤተሰቦቹ፣ ከአዲስ አበባ)