Friday 28 March 2014

ኢትዮጵያዊነት ለእኔ !

                              ኢትዮጵያዊነት ለእኔ !
ከአፈወርቅ በደዊ

      ኢትዮጵያዊነት ለእኔ በቀለበት ይመስላል። ቀለበት ፈርጥ ካለው ያምራል ። ያለ ፈርጥ ግን አያምርም ። ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ጎሳዎች የቀለበት ፈርጥ አንጂ ቀለበት አይደሉም  ። ህልውናቸው ከቀለበቱ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው ። ቀለበት ከሌለ ፈርጥ የለም ። ኦሮሞ፣ አማራ ፣ትግሬ፣ወላይታ፣ጋምቤላ፣ጉምዝ እና ሌሎችም እያልን በሃገሪቷ ውስጥ ያሉትን ጎሳዎች በጠቅላላው ብንዘረዝር የሃገሪቷ ውበቶች ወይም ፈርጦች ናቸው።
     እያንዳንዱ ጎሳ እና የጎሳ አባል ማወቅ የሚገባው ዋና ነገር ጎሳው ኢትዮጵዊ በመሆኑ ያገኘው ገፀ-በረከት እንጂ መርጦ እና ፈቅዶ ያለመሆኑን ነው። እኔ ኦሮሞነቴን ወይም አማራነቴን ያገኘሁት ኢትዮጵያዊ በመሆኔ ነው ብሎ ማስብም ሆነ ማመን ያስፈልጋል ። ይህ ባልሆነበት ሁኔታ እኔ ኢትዮጵያዊ ባልሆንም ኦሮሞ ፣አማራ፣ ወይም ትግሬ ወይም ሌላ ጎሳ መሆን እችላለው የሚል ግንዛቤ እውነትነት የሌለው የትም የማያደርስ መንገድ ነው። አንዳንድ ያወቅን  የነቃን የጎሳ አባላት ነን የሚሉ « አላዋቂ አዋቂዎች  ወይም አለማወቃቸውን የማያውቁ አዋቂዎች » ማንነታቸውን እረስተው የሚያራምዱት መርዘኛ አስተሳሰብ የትም አያደርስም።   
 ᎐᎐᎐ ይቀጥላል ᎐᎐᎐
ሙሉውን ለማንበብ ከታች ያለውን link በመጫን ገፅ 16 ያንብቡት ᎓᎓

ክብር ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያን ይሁን !!!
                                                                                                  Posted by A.G



No comments:

Post a Comment