Sunday 20 December 2015

አዲስ አበባዎች ሊነሱ ነው !

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚከተሉትን መፎክሮች አንግበው መንግስት በአገሪቱ ላይ እየወሰደ ያለውን መንግስታዊ ውንብድና ለመቃወም እየተዘጋጁ መሆናቸው ታወቀ፡፡ የውስጥ ወሬ ምንጮቻችን እነደገለፁት መቸ በይፋ እንደሚጀምሩት በምስጥጢር ተይዝዋል በማለት ክፍለ ሀገር ያሉ(በኦሮሚያ፣በአማራ፣በደቡብ፣…) የተጀመረውን ትግላቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡
ማህበረሰቡ፡- 1. በኦሮሚያና በአማራ እየተደረገ ያለው ደም ማፋሰስ ይቁም!
                2. በልማት ስም ህዝብን ከይዞታቸው ማፈናቀሉ ይቁም!
                3. መሬት የህዝብ እንጂ የመንግስት አይደለም!
                4. የብሄር ፖለቲካ ይቁም! ሆን ተብሎ ብሄርን ከብሄር የማጋጨት ሴራው ይምከን!
                5. መንግስት የከፋፍለህ ግዛው ስትራትጅውን ያቁም!
                6. በርሀብ አለንጋ እየተገረፉ ያሉ ዜጎች አስቸኳይ መፍትሄ ይሻሉ!
                7. የታሰሩ የፖለቲካና የህሌና እስረኞች ይፈቱ!
                8. የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ወደቦታው ይመለስ!
                9. የፍትህ ስርአቱ ይስተካከል!
               10. መንግስት አይን ያወጣ ውሸቱን ያቁም!
               11. መሰረት የሌላቸው መግለጫዎች፣የውሸት ፕሮፖጋንዳዎች፣ዛቻና ማስፈራሪያዎች ይቁሙ! ህዝቡ እውነቱን                          የውቃል! ማንም
 አያምናችሁም!                               
               12. ኢህድግ የሚሰማ ጀሮ፣የሚያይ አይን የለውም! በእብሪት ተወጥሯል!
               13. ኢህድግ የበሰበሰ ድርጂት ነው! ህዝብን ማሰተዳደርና አገርን መምራት ተስኖታል!
               14. ታፍነን አንግዛም፣አባቶቻችን አላወረሱንም!
               15. ዝርፊያው ይቁም!ሙሰኞችና ኪራይ ሰብሳቢዎች ለፍርድ ይቅረቡ!
               16. በጎንደር ዳርቻ ለሱዳን በሚሥጥር የተሰጠው መሬት ይመለስ!
               17. አሸባሪው ህዝብ ሳይሆን መንግሰት ነው!
               18. አሰመሳይ መንግስት ሊሆን አይችልም!
               19. የአንድ ብሄር የበላይነት ይቁም!
               20. መንግስት ውሸት፣ማጭበርበር እና ሌብነትን ባገሪቱ ላይ አንግሷል!
               21. ባገሪቱ ላይ ያሉ አደገኛ እፆች(ጫት፣ሲሻ፣አሸሽ፣…) ይወገዱ! መንግስትም ከማምረት ይቆጠብ!
               22. ህገመንግስቱ ይከበር! አፋኝ ህጎች ይሻሩ!
               23. ህንፃ፣ባቡር፣… ለኛ ምናችንም አይደለም፤በቅድሚያ ነፃነት!
               24. መንግስት የግል ጥቅሙን ትቶ በአገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ የጋራ ውይይት ይጥራ! ከማንኛውም ተቃዋሚ                     ሀይል ጋር ብሄራዊ እርቅ ያካሂድ!
              25. የሽግግር መንግስት ይቋቋም! ፍትሀዊ ምርጫ እንደገና ይካሄድ!
              26. ዳግመኛ ደርግን አናስተናግድም!

ተማሪዎች፣መምህራን እና የመንገስት ሰራተኞች፡-
              1. መንግስት ማህበረሰቡን ማጋጨት ያቁም!
              2. በማህበረሰቡ ላይ የሚደረገው ማዋከብ ይቁም!
              3. ፍታዊ የሀብት ክፍፍል ይኑር!
              4. በአገሪቱ ላይ ወጥ የሆኑ መመሪያች ይኑሩ!
              5. የትምህርት ጥራት ይጠበቅ!
              6. መልካም አስተዳደር እንሻለን!
              7. የታክስ ማሻሻያ ይደረግ!
              8. የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ!
              9. የአርከን ጭማሪ ይፈቀድ!የደረጃ እደገቱ ማሻሻያ ይደረግ!
             10. የውሎ አበል፣የትርፍ ሰአት ክፍያ፣የትራንስፖርት እና የቤት አልዋንስ ይሻሻሉ!
             11. ስራ ቅጥር/ስልጣን በደብዳቤ ሳይሆን በውድድር/በብቃት ይሁን!
             12. መንግሰት የውሸት ድራማ መስረቱን ያቁም!
             13. መንግስት ከመንገድ/ከህንፃ ይልቅ በቅድሚያ ማህበረሰቡን ያልማ!
             14. መንግስት ነጋዴ ነው!
             15. መንግሰት የህዝብ አገልጋይ አንጅ ህዝብ የመንግሰት አገልጋይ መሆን የለበትም!
             16. አገሪቱ “አርቲፊሻል” እድገት ላይ መመስረት የለባትም! ማጭበርበሩ ይብቃ!
             17. ከ2 ጊዜ በላይ ታክስ እየተደረግን ነው! (ደመወዝ ሲከፈል-የስራ ግብር፣እቃ ስንገዛ-ቫት እና የሰርቪስ አገልገሎት፡፡ ስለሆነም 35%+15%+5%=55% ደመወዛችን ታክስ ይደረጋል!)  በቃ! በቃ! በቃ! በቃ! በቃ! በቃ!………………..
እነዚህን መፎክሮች በጋራ በማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እነዳሰቡና መንገስት ለሚወስደው ማንኛውም እንቅስቃሴ እነደማይታገሱትና የመግደል ሙከራ ካደረገም አስፈላጊውን ምላሽ እነደሚያደርጉ ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ አንደሆነ በምሬት ተናግረዋል፡፡ 
 ማንም ሀይል እነደማያደራጃቸው የገለፁ ሲሆን የአመፁ መንስኤ የመንግሰት ብልሹ አሰራር፣አፈና፣ማዋከብ፣ መግደል፣ማፈናቀል፣ግፍ፣አድሎ፣ማሰር፣የኑሮ ውድነቱ፣ፍትህ ማጣቱ፣ብሄርን ከብሄር ማጋጨቱ፣የስነ ልቦና ጫናው ተደማምረው ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት ስለፈጠሩባቸው ከዚህ የባሰ ምን ይመጣል ወይ ሞት ወይ ነፃነት በማለት ከሰፊው የኢትዮጵያ ማሀበረሰብ ተቃዋሚዎችጋር ለመቀላቀል እነደወሰኑ ለወሬ ምነጫችን ተናግረዋል፡፡
የመንግስትን ሀይል ለመቋቋምም ሰላማዊ አመፁ ለሊት ላይ በመጀመር መንግሰትን አከርካሪውን ለመስበር አስበዋል፡፡ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል (ሴት፣ወንድ፣ አዋቂ፣ህፃን፣አረጋውያን፣ የሀይማኖት አባቶች፣መምህራን፣የቢሮ ሰራተኞች፣ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ሹፌሮች፣ነጋዴዎች፣ጎዳና ተዳዳሪዎች፣ተማሪዎች….) ወደ ጎዳና መውጣት የመጀመሪያው የሰልፉ/የአመፁ ምእራፍ ነው፡፡ ማንኛውንም ንብረት ማውደም “በህግ” የተከለከለ
ነው፣ከላይ የተዘረዘሩትን መፎክሮች ማሰማት ብቻ በቂ ነው፡፡ መምህራንና የመንግስት ሰረተኞችም ከሚቀጥለው ሰኞ ጀምረው የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉም አበክረው ገልፀዋል፡፡መቸም ቢሆን ከዚህ በኋላ ትግሉ እንደማይቆም አክለው ገልፀዋል!!
በተጨማሪም ከህዝብ አብራክ የወጣውን ፌድራል ፖሊስንና መከላከያ ሰረዊትን ከጎናቸው እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡
ሼር በማድረግ የትግሉ አጋር ይሁኑ!
ድል ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!!!!!.

No comments:

Post a Comment