Monday 10 November 2014

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ከፍተኛ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ የነበሩት ረዳኢ ገ/አናኒያ ከስልጣናቸው ተነሱ

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ከፍተኛ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ የነበሩት ረዳኢ ገ/አናኒያ ከስልጣን መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። የሕወሀት አባል የሆኑት ረዳኢ ከ1985ዓ.ም ጀምሮ የክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ሃላፊ በመሆን በመቶ አለቃ ማዕረግ እስከ 1993ዓ.ም ደረስ ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
ፓርቲው ለሁለት ሲሰነጠቅ በመለስ ዜናዊ ታማኝ ሆነው ከተመረጡት አንዱ የሆኑት ረዳኢ በፌዴራል የልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው መሾማቸውን ምንጮቹ አስታወሰዋል። ቀጥታ ተጠሪነታቸው ለጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እንደነበር ሲታወቅ በመቀጠል የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ ተደርገው ተሾሙ። በ1997-98 በዜጎች ላይ ለደረሰው የጅምላ ግድያና እስር እንዲሁም ስቃይ ከመለስ ትእዛዝ በመቀበል ሲያስፈፅሙ የነበሩት ረዳኢ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።
በበርካታ ሰላማዊ ወገኖች ላይ ተመሳሳይ ግፍ ያስፈፅሙ እንደነበረ አክለዋል። ረዳኢ በ10 ሚሊየን የሚቆጠር ሃብት በሙስና እንዳከማቹ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። ከስልጣን የተነሱት ለመለስ ታማኝ ስለነበሩ ነው ብለዋል ምንጮቹ። ረዳኢ ወደ አሜሪካ ለመምጣት ሃሳብ እንዳላቸው እዚህ ከሚኖሩ የቅርብ ወዳጃቸው የተገኘው ጥቆማ ያመለክታል።

No comments:

Post a Comment