Monday 10 November 2014

ለአንድ ወር የጠፋችው የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አስከሬን ከነመኪናዋ ጭቃማ ኩሬ ውስጥ ተገኘ

(ዘ-ሐበሻ) የቴክሳስ ፖሊስ ከኦክቶበር 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የጠፋችውን ኢትዮጵያዊት እናት አስከሬን ከሃይቅ ያነሰ ውሃ (ኩሬ) ውስጥ ከነመኪናዋ ገብታ ማግኘቱን አስታወቀ::

almaz
በመዲ ክሬክ የገበሬዎች ከሃይቅ አነስ ያለ ውሃ ውስጥ አንድ ቫን መኪና የተገኘ ሲሆን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ ገብረመድህንን ሰውነት እንዳገኘ ጠቁሟል:: የወ/ሮ አልማዝ ሰውነት የተገኝበት ጭቃማ ኩሬ የሚገኘው ከምትሰራበት ቦታ በ3 ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው:: ፖሊስ የአልማዝ ሰውነትን ከነ ሼቭሮሌት መኪናዋ እንዳገኘ ለቤተሰብ ያስታወቀ ሲሆን አሁን እንዴት መኪናው እዚያ ውሃ ውስጥ እንደገባ በምርመራ ላይ ይገኛል::
ተጨማሪ መረጃ ተመልሰን ይዘን እንመጣለን…
-- Ze-Habesha
ተጨማሪ ምንጭ 

No comments:

Post a Comment