Tuesday 31 March 2015

አውቀው ነው ስደተኞቹን የደበደቡት

በግሩም ተ/ሀይማኖት

ለሞቱት 46 ኢትዮጵያዊያ ሳዑዲ ተጠያቂ ናት…መደብደቧን አመነች

ትላንት ንጋት ላይ በሰሜናዊ ምስራቅ የመን ሀጃ አካባቢ በተደረገ የአየር ድብደባ አየር የ International Organization for Migration (IOM) ካምፕ ላይ ጥቃት ያደረሱት የሳዑዲ አረቢያ የቶር ጀቶች መሆናቸው ታወቀ፡፡ የሳዑዲ መንግስት ባለስልጣናትም ድብደባው በእነሱ ጀት መፈጸሙን አምነዋል፡፡ ድብደባው ግን ሆነጅ ተብሎ የተፈጸመ እንደሆነ የሚያሳይ ፍንጭ አለ፡፡ ቦታው የ UNHCR ካምፕ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ የ UNHCR አርማ ያለበት ድንኳን የተጣለበት መሆኑ እና የ UNHCR አርማ እየተውለበለበ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በእስከ አሁን ሁኔታ በጨለማ ሲደበድቡ ቅንጣት ስህተት አልነበረም፡፡ 


በሌላ በኩል ደግሞ አርማውን አላየንም አይባል ድብደባው የተፈጸው ንጋት ላይ ነው፡፡ አንዴ ሳይሆን በተደጋጋሚ ነው እየተመላለሱ የመቱት፡፡ ይሄ ምን ያሳያል እስኪ መንግስት ካለን መብታችንን የሚጠይቅልን ከሆነ ይሄን ይጠይቅ…..እባካችሁ ወገን እያለው ወገን እንደሌለው ሀገር እያለው ሀገር እንደሌለው የትም እየረገፈ ላለው ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ድምጽ እናሰማ፡፡ እባካችሁ የተኙትም ይንቁ ጠግበው ተገልብጠው እያደሩ ወገን እነሱ ባንኮራፉ ቁጥር እየረገፈ መሆኑን ይወቁት ይህን የሰው ልጅ ላይ የደረሰ አሰቃቂ እልቂት ያላየ ይይ ሼር አድርጉ……..በሁኑ ሰዓት የአየር ጥቃቱ ከወታደራዊ ተቋም ወደ ሲቪሉ ህዝብ እየወረደ ነው፡፡ በርካታ ሲቪሎች እየሞቱ ነው፡፡


በጣም የሚያሳዝንና ዘግናኝ አሟሟት ያዘለ ፎቶ ለመመልከት ይህን ይከፈቱ

No comments:

Post a Comment