Monday 16 March 2015

በሳውዝ አፍሪካ ደርበን ከተማ የወያኔ|ኢህዲግ ኢንባሲ ትልቅ ውረደት ገጠመው።


የተለመደ የማጭበርበር አላማውን (የቦንድ፣ የኮንዶሚንየምና የመሬት ሽያጭ ) አጀንዳውን ይዞ ሕዝቡን ለመሰብሰብ ባለፈው ቅዳሜ ደርባን የተገኘው የኢትዮጲያ ኢንባሲ ተቃዋሚዎች በበተኑት የተቃውሞ ቅስቀሳ መሰረት በህዝቡ የነበረውን ስሜት በመረዳታቸው ህዝቡን መሰብሰብ አልቻሉም ነበር። ይልቁንም ቅዳሜ ማታ የየራራሳቸውን ልጆችና አንዳንድ ለጥቅም ያደሩ 
ልጆችን በተናጠል እያስጠሩ አልጋ በያዙበት ሆቴል ፎርም ሲያስሞሉና ብር ሲዘርፉ አድረዋል። በቀጣዩ ቀን እሁድ ጠዋትም አንድ  ኤፍሬም በሚባል ግለሰብ ለጥቅም አድሮ ህዝቡን ለመንግስት ወንበዴዎች በሚያዘርፍ የአበሻ ምግብ ቤት ወስጥ መኖራቸውን  መረጃ ያገኙ የተቃዋሚ ሀይሎችና ሀገር ወዳድ ኢትዮጲያውያን በነቂስ በመገኘት የተለያዩ መፎክር በማሰማት ተቃውማቸውን  አሰምተዋል። ተቃውመው እየጠነከረ መሄዱን የተረዱት እነዚሁ የወያኔ ጉጅሌዋች ከአበሻው ምግብ ቤት ወጥተው በመኪናቸው  ገብተው ለማምለጥ ሲሉ መኪናቸው በእንቁላልና በድንጋይ ተደብድቧል። ከወያኔዎችም ከመኪና ውስጥ ተጎትቶ ቦክስ የቀመሰም እንደነበር ታዝበናል
የህዝቡ ቁጣ ከፍተኛ በመሆኑ መኪናቸውን አስነስተው በፍጥነት ባይሸሹ ኑሮ ከዚያ የበለጠ አደጋና ውርደት ይገጥማቸው ነበር።
ወያኔን በሔደበት ማዋረድ ይቀጥላል።



No comments:

Post a Comment