Sunday 4 January 2015

ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ታጋዮች ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ ህዝብ ጎን በመሰለፍ በዘረኛውን ናዚ ወያኔ መከላከያና ከትግራይ ተስፋፊ ታጣቂዎች ጋር ከባድ ውጊያ አያካሄደ ይገኛል።አዴሃን ከኤርትራ/ሻቢያ/ ምድር ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለውጤት የሚያበቃውን የአደረጃጀት ስልት በመንደፍ /በመቀየስ/ ወደ ተጨባጭ ስራ መግባቱን ይፋ ማድረጋችን ይታወሳል።
አዴሃን በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም የወያኔ ስርአት አረመኔያዊ አገዛዝ ግፊት ቀማሽ ለሆነው ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ አካባቢ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተንቀሳቀሰን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም ህውሃት በወረራ የያዛቸውን የወልቃይት ጠገዴና የአርማጭሆ ሰፋፊ ለም መሬቶችን አስተማማኝ ለማድረግ እና አዳዲስ መሬቶችን ለመያዝ የነደፈውን እስትራቴጂ ተግባራዊ ሊያደርግ እየተዘጋጀ መሆኑንና ታላቋን ትግራይ ለማስፋት ባለው ህልም መሰረት ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን August 19 – 2014 ” ህወሃት በወልቃይትና ጠገዴ ህዝብ ላይ ተጨማሪ የዘር /ማጽዳት/ፍጅት ለማካሄድ እየተዘጋጀ ነው።” በሚል ርዕስ መረጃዎችን ይፋ አድርገን ነበር።
በሌላ በኩልም November 19- 2014” የጠገዴ ወረዳ ህዝብ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም በማለት እራሱን ለመከላከል እየተዘጋጀ ነው።” በሚል ርዕስ ለህዝብ የተበተነውን የትግል ጥሪ ፓምፕሌት ጨምረን ይፋ አድርገን እነደነበር ይታወሳል። በመሆኑም ወያኔ የትግራይን የመስፋፋትና አማራውን የማጥፋት አባዜውን እውን ለማድረግ፦ ህዝቡም እራሱን ለመከላከልና ማንነቱን ለማስከበር በጀግንነት ዱር ቤቴ ብሎ የራሱን የጎበዝ አለቃ መርጦ በከባድ መሳርያ የሚታገዘውን የወያኔ ሰራዊት በከፍተኛ ደረጃ እየመከተ ይገኛል። በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም በቅርብ የሚገኘው አማራውና እንዲሁም በተለያየ መንገድ ወያኔን ለማሰወገድ በትግል ላይ ያሉ ድርጅቶች ከህዝብ ትግል ጎን እንዲቆሙ አሳስበንም ነበር። ይኸው ዛሬ የወያኔ የጸጥታ መከላከያና፡ የትግራይ ታጣቂዎች እንዲሁም ስውር ነብስ ገዳይ ደህንነቶች በማን አለብኝነት በሰላማዊ ህዝብ ላይ ከታህሳስ 17- 2007 ጀምሮ ግልጽ ጦርነት ከፍተዋል። ህዝቡም እራሱን ለመከላከል ሲል በሚቻለው ሁሉ ራሱንና ሀገሩን ከባዳዎች ስብስብ ለመከላከል ዘረኛውን አባገነን ስርአት እየተፋለመው ይገኛል።
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ታጋዮችም ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተልን ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ ታረካዊ ግዳጃችንን እየተወጣን እንገኛለን። በአሁኑ ጊዜ አረመኔው የወያኔ ስርአት በርካታ የመከላከያ ሃይሉን ከትግራይ ግንባሮችና ከመሃል ሀገር ሳይቀር ወደ ስፍራው በማንቀሳቀስ የሚያካሄደውን የማንነት ትግል በሃይል ለመጨፍለቅ እርብርብ እያደረገ ይገኛል ። በተለይ የናዚው ወያኔ የግፍ አገዛዝ ሰለባ ላለመሆን እራሳቸውን መከላከል የማይችሉትን ህጻናት፣ ሽማግሌዎችንና ሴቶች ላይ አረመኔያዊ የሆነ ጥቃት እየፈጸመ ይገኛል።አሁን ባለንበት ሰአት የወልቃየት ጸገዴና አርማጭሆ ህዝብ በከፍተኛ ወኔ እየተጠራራ እየተደራጀ የጀመረውን የነጻነት ትግል ለማጠናከር ዱር ቤተ ብሎ ከያለበት የእከተተ ይገኛል ።
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄም የቻለውን ሁሉ በማድረግ ከህዝቡ ጎን ተሰልፎ የራሱን ታሪካዊ አስተዋፆ በማበርከት ህዝቡን የድል ባለቤት ለማድረግ ተግቶ በሰራት ላይነው ። ሁኔታው የሚመለከታችሁና የሚያሳስባችሁ ወገኖች ሁሉ የተቀጣጠለውን ካለው ህዝባዊ ትግል ጎን እንድትሰለፉ አዴሃን ወቅታዊ ጥሪ ያቀርባል።በሁሉም መስክ ትግሉን ለማጠናከር በየቀኑ ሁኔታውን በመከታተል፣ እንድትሳተፉ በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
፠ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ፠
ሞት ለወያኔ
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ስ\አስፈፃሚ


No comments:

Post a Comment