Wednesday 7 January 2015

የኢሳት ጋዜጠኞች መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም አስመራ ገቡ


የኢሳት ጋዜጠኞች መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም አስመራ ገቡ
(ዘ-ሐበሻ) ኢሳት በሰበር ዜና እንዳቀረበው ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ከዋሽንግተን ዲሲ እንዲሁም ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ከሆላንድ ኤርትራ ገቡ::
ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም
ከኢሳት እንደተገኘው መረጃ ከሆነ ጋዜጠኞቹ አስመራ የገቡት ትናንት ሲሆን በኤርትራ ቆይታቸውም እዚያ ያለውን ሃይል እንደሚጎበኙና ዘገባም እንደሚያቀርቡ በተጨማሪም የኤርትራ ባለስልጣናትን እንደሚያነጋግሩ ይጠቁማል::

የቀድሞው የጀርመን ድምጽ ጋዜጠኛና የአሁኑ የኢሳት ራድዮ ከፍተኛ አዘጋጅ መሳይ መኮንን; እንዲሁም የቀድሞው የአዲስ ዜና ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የአሁኑ የኢሳት ቲቭ ኤዲተር ፋሲል የኔዓለም በአስመራ ለስንት ጊዜያት እንደሚቆዩ እስካሁን የተገኘ መረጃ የለም::

No comments:

Post a Comment