Wednesday 18 February 2015

የየካቲት 12 አርበኞቻችን እና ሰማዕታት በዘመኑ ፖለቲካችን እይታ

ታሪክ ምን ያስተምረናል ?

'''ታሪክ ምን ያስተምረናል?''ተብሎ ለተጠየቀው ጥያቄ ''ታሪክ የሚያስተምረን የሰውልጅ ከታሪክ  ምንም አለመማሩን ነው'' ብሎ የመለሰ አንድ ምሁር እንደነበርአስታውሳለሁ።የካቲት 12 /1929 ዓም አዲስ አበባ  ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ  አንዲት ጀንበር ሰማአትነት የተቀበሉባት ቀን ነበረች። ዛሬ ዛሬ ይህ ቀን  ከተማዋከንቲባ ጉንጉን አበባ ከማስቀመጥ እና አንዳንድ ከከተማዋ በዘለለ አስከ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማይሰሙ 'ኤፌምየራድዮ ጣብያዎች ፕሮግራሞች  ከመቅረባቸው ባለፈታሪኩ ላሁኑ ትውልድ  በተገቢው መልክ ታሪኩ እየተነገረው አይደለም።ይህ ታሪክ ግን አስተማሪነቱ ዘርፈ ብዙ ነው።የሀገራችን ባለጊዜ ፖለቲከኞች መልሱ ለከበዳቸውአንዳንድ ክስተቶች የየካቲት 12 አይነት ታሪኮችን  ትውልዱ በማስተማር ቁም ነገር በሰሩበት ነበር። ለመሆኑ  ዛሬ ሰባ ስድስት ዓመት አዲስ አበባ ምን ሆነች?ብዙዎቻች ታሪኩን የምናውቀው የሚመስለን ግን አውቀነውም ቁምነገሩን እና አንደምታውን ችላ ያልነው ጥቂቶች አይደለንም። የዛሬ ሰባ ስድስት ዓመት አብርሃም፣ሞገስ ስምዖን በግራዝያን ላይ ባቀናበሩት  ቦንብ አደጋ (ጣልያን አሸባሪ ብሎአቸው የነበረ መሆኑን ሳንረሳየጣሉበት እና አዲስ አበባ  ደም ጎርፍ የታጠበችበት  መከራቀን-የካቲት 12/1929

አብርሃም ደቦጭ  ሞገስ አስገዶም   ስምዖን አደፍርስ  ማናቸው?
 አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1936 (1929 ዓም )   ዓለም ፖለቲካ ብዙ አዳዲስ ክስተቶች የታዩበት ነበር።
- የጣልያኑ ፋሺሽት መሪ ሞሶሎኒ   ሮማ 'ኤምፓየር' አዲስ መሬት   አዲስ አበባን መያዙን  ያሳወቀበት፣ ቀደም ብለው ተግባሩን  አደባባይም ሆነ  በስውርም ሲደግፉየነበሩ ሀገሮች ማንነታቸው የለየበት፣
 -  ብሪታንያ ዜና አገልግሎትቢቢሲየመጀመርያ  ቴሌቪዥን ፕሮግራሙን  የጀመረበት፣ 

 -  አሜሪካው ፕሬዝዳንት  ሩዝቬልት  ሁለተኛ ጊዜ የተመረጡበት 
 -  ጃፓን ባህር ኃይል  ቻይናን ሻንጋይ ክፍለ ሀገር የወረረበት  እ ባጠቃላይ ጊዜው ዓለም ወደ     ሁለተኛው ታላቁ ጦርነት ለመግባት አራት አመታት ብቻ ቀርቷትየምትታትርበት ጊዜ ነበር።

አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም ሐማሴን አና አካለ ጉዛይ (አሁኗ ኤርትራ)ተነስተው በፋሺሽት እጅ የወደቀችው  የሀገራቸውን   ኢትዮጵያ አርበኞች ሊቀላቀሉመጡ። ከለበሱት ልብስ ውስጥ ኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አጥፈው ይዘዋል።ህልማቸው፣ሳጋቸውን እየተናነቀ  የሚይዛቸው  ሀገራቸው መከራ እረፍት ነሳቸው።በወቅቱ ከነበሩት ትምህርትቤቶች  ጣልያንኛ  ተምረው ስለነበር  ቅኝ ግዛት ችግርን  ሀገራቸው ኢትዮጵያ ላይ የሚያመጣውን አንደምታ  ጊዜው ፖለቲካ ጋርአዛምደው መረዳታቸው  ሌላው የ እግር ውስጥ እሳት ነበር  እዚህ ጊዜ ነበር እንደነሱ በሀገሩ ጉዳይ ውስጡ ይንተከተክ የነበረውን ስምዖን አደፍርስን  ያገኙት።

ስምዖን አደፍርስ ''በመናደድ ብቻ መቆም የለብንም  ወሳኝ የሆነ ሥራ መስራት አለብን ፋሽሽትን ደሞ ትጥቅ ትግል በቀር ምንም ሌላ መንገድ የሚዋጋው  የለም''ይላቸው ነበር። ስምዖን አደፍርስ ገና የከተማ መልክ አየያዘች በነበረችው አዲስ አበባ ውስጥ ጅቡቲ ይኖር ከነበረው ወንድሙ በተላከለት ታክሲ  ሥራ ላይ ነበር። ስራው ላይ አያሌ  ፋሺሽት ጣልያኖች ግፍ  በደል እ  ሃገሩ የወደፊት እጣ ሲያስበው ንዴት ፣ውርደት  አልገዛም ባይነት አንድ ላይ ተደባልቀው ውስጡንአናውጠውታል። ይህን ስሜት ይዞ ነበር ሌሎቹ  ሀገራቸው  ኢትዮጵያ ፍቅር ያንገበገባቸውን ሁለቱን ወጣቶች አብርሃም ደቦጭ  ሞገስ አስገዶምን ያገኛቸው።
''እልል በሉ ልእልት  ተወለደች ''
አብርሃም፣ሞገስ አና ስምዖን  አዚህ ሃሳብ ላይ ሳሉ  ነበር ሞሶሎን ኢትዮጵያ ሹመኛ ግራዝያን'' ልእልት ተወለደች ተሰብሰቡ ፣ቸርነቴን ተመልከቱላብላችሁ፣ላጠጣችሁ''ብሎ አሁኑ ስድስት ኪሎ ዩንቨርስቲ የያኔው አፄ ኃይለስላሴ ቤተመንግስት አዲስ አበባን ሕዝብ የጠራው። ይህ አጋጣሚ  እነ አብርሃምታላቅ አጋጣሚ ሆነ። ድግሱ ላይ ንግግር እንደሚያደርግ  የሚጠበቀው ግራዝያን ላይ የእጅ ቦንብ ወርውረው መግደል የሚል አቅድ አዘጋጁ። እዚህ ሃሳብ ደግሞ እጅቦንብ አጠቃቀም መማር ያስፈልጋል። ስምዖን ደጃዝማች አፈወርቅ ወታደሮች በድብቅ አንዲያስተምሯቸው ሁኔታውን አመቻቸ። በየቀ ወደ ስፍራው  አዲስ አበባ ውጭ ከሁለት ሰዓት በላይ በታክሲው  እየወሰደ አስተማራቸው  ቀኑ ደረሰ።በአቅዳቸው መሰረት ሞገስ እ አብርሃም ግራዝያንን ቦንብ  ገደሉ በሁዋላ  አሁኑ ቅዱስማርቆስ ቤተክርስትያን አጥር በኩል ይዘሉና ቆሞ  የሚጠብቃቸው ስምዖን ታክሲ ውስጥ ገብተው አዲስ አበባ መውጣት ቀጥለውም ሰሜን ሸዋ ላይ በውጊያ ላይ ካለውራስ አበበ አረጋይ አርበኛ  ጦር ጋር መቀላቀል እ መዋጋት የሚል  ታላቁ አቅድ ብለው መከወን ተግባራቸው ሊሆንቃል ለምድር ለሰማይ 'መሀላቸው  ነበር።

የካቲት 12 /1929 ዓም  ''ደም እንደ  ውሃ ''
የካቲት ከገባ ገና አስራ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።የ አዲስ አበባ አየር ደመናማ ነበር። የተለመደው በልግ ዝናብ ሊመጣ ዳር ዳር የሚል ይመስላል። አዲስ አበባ መንገዶችጣልያን ወታደሮች ይታመሳል። ሰሜን ሸዋ ላይ የሚዋጋው አንዳንዴም አዲስ አበባ መግብያ በር ደረሰ እየተባለ የሚወራለት  አርበኛው ራስ አበበ አረጋይ ሰራዊት ጠጅ ቤቱ በ ቅኔ አዘል ግጥም ይሞገሳል። ቅኔው የገባቸው ባንዳዎችም አዝማሪውን እየጠቆሙ ፍዳውን ያሳዩታል። አዝማሪው ገና አለ ገና በሚል መልክ ውግያውይቀጥላል የሚል ቃና ያለው ግጥም  ያንቆረቁራል-

 '' የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣
  ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ''

እየተባለ ሴት ወንዱ ውጊያ የተዘጋጀበት አርበኛ ሆኖ መሞት የተናፈቀበት  ጊዜ ነበር። ስድስት ኪሎ የያኔው ቤተመንግስት አሁኑ ዩንቨርስቲ አዲስ አበባ በግድም በውድም በተሰበሰቡ ባብዛኛው ሴቶች  ሕፃናት ተሞላ። እብሪት የተሞላበት ግራዝያኒ ንግግር ተጀመረ። በንቀት ያየው ሕዝብ ላይ ስለ ''ታላቂቱ ጣልያን'' መደስኮርጀመረ። ግን ብዙ አልቆየም አብርሃም እ ሞገስ ሕዝቡን ጥሰው ከፊቱ ደረሱ ሰባት ቦንቦችን አከታትለው ወረወሩበት፣ግራዝያን ቆሰለ፣  አየር ኃይሉ ኃላፊ ተገደለ።አብርሃም እ ሞገስ  ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን በኩል ባለው  ቤተመንግስቱ  ጋራ  አጥር ዘለው ወጡ እ ታክሲ ይዞ ወደሚጠብቃቸው ስምዖን ገሰገሱ፣ ስምዖንበታክሲ ወጣቶቹን ይዞ ነጎደ፣ እንጦጦ ተራራ ላይ ውጥተው አዲስ አበባን ቁልቁል አይዋት፣ ግራዝያን በቆሰለበት ሆኖ አዋጅ አውጆ ለካ  አዲስ አበባ ወንድ ሴት ሕፃንአዋቂ ሳይባል  ጥይት፣በ አካፋ እ ዶማ በተገኘው ሁሉ መፈጀት ተጀምሯል።
ሶስቱ ወጣቶች ተቃቅፈው ተላቀሱ።ጊዜው እስኪመሽ ጠበቁ እ ስምዖን ወደ ደብረሊባኖስ ይዟቸው ነጎደ።ለ ሰሜን ሸዋ ራስ አበበ አረጋይ ቅርብ የሆነችው -ደብረሊባኖስአመቺ መስመር እንደሆነች ሁሉም አምነውበታል። ስምዖን ተልኮውን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። አብርሃም  ሞገስ  ራስ አበበ አረጋይ ጦር ጋር ተቀላቀሉ።

የካቲት አስራ ሁለት ቀን አዲስ አበባ ብቻ  ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ ሰማአትነት ተቀብለዋል። ብዙ  የሚቆጠሩ ቤቶች ተቃጥለዋል። ግድያው በመንገድ ላይ የተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ ሲሆን ለመግደል  የሚፈለገው መስፈርት ኢትዮጵያው መሆኑ ብቻ ነበር።



 አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚገኘው  የካቲት 12 የሰማዕታት ሃውልት

 አብርሃም ፣የ ሞገስ  ስምዖን  ሀገር ፍቅር እስከ መቃብር

ስምዖን 
ምዖን አብርሃም እ ሞገስን ደብረሊባኖስ ወደ ሰሜን ሸዋ መንገድ ከሚያውቃቸው አርበኞች ጋር አገናኝቶ ተመለሰ።ብዙም አልቆየ ፋሽስቱ ጥቁር ለባሾች ተይዞ ብዙ መከራ እና ስቃይ ተገደለ። የታሪክ ምሁራን እንዳስቀመጡት ስምዖን እጁም ሆነ እግሩ ጥፍር በጉጠት እየተነቀለ ጣቶቹን እየሰባበሩ አሰቃይተው ገደሉት።
አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም 
አብርሃም ደቦጭ  ሞገስ አስገዶም ራስ አበበ አረጋይ አርበኞች ጦር ጋር ከተቀላቀሉ በኃላ ራስ አበበ አረጋይ ልዩ እንክብካቤእንዲያገኙ አደረጉ።ቆይተው ግን የነበራቸውን ትምርት ደረጃ በመረዳት ሀገር ውጭ ወጥተው ሀገራቸው ቢሰሩ ይጠቅማሉ ብለው በማሰብ ስንቅ እ ገንዘብ ጋር ወደሱዳን እንዲሄዱ መከሯቸው። ሆኖም  ግን ጉዞአቸው ላይ ሱዳን ሊገቡ ትንሽ ሲቀራቸው  ፎቶዋቸው ገጠር ባሉ ፋሺሽት ወታደሮች ሁሉ ተናኝቶ ነበርና ፋሺሽቶች ተይዘው በስቅላት ሰማዕት ሆኑ።በኃላ ግን አፄ ኃይለሰላሴ  ሱዳን በኩል ጣልያንን እንግሊዝ ሰራዊት ጋር ሆነው ድል ሲያደርጉ  አብርሃም እ  የሞገስ አስከሬንተቆፍሮ ወጥቶ አሁን አዲስ አበባ በሚገኘው  ቅድስት ስላሴ አርበኞች ሃውልት ስር እንዲያርፍ አድርገዋል።

''ዘመኑን ዋጁት''
ዛሬ ላይ ሆነን ዛሬ ሰባ ስድስት ዓመት የነበሩትን ወጣቶች ስናስብ እ ሐማሴን  አካለጉዛይ  እኛ ኢትዮጵያውያን የተለዩ አስመስለው ሊያወሩን ለሚፈልጉ መረብማዶም ሆነ ከመረብ ወዲህ ላሉት ባለ ጊዜዎች ትንሽ ጊዜ ወስደው እንዲያስቡ ማረግ ተገቢ ነው። መረብ ማዶውን መረብ ወዲሁ የተለያየው ታሪክ፣በ ዘር፣ ሃይማኖት ሳይሆን ባለጊዜዎች በፈጠሩት ተረት ታሪክን ከ ጥቅማቸው ጋር  አየበወዙ  ኪስ ማደለቢያ ስላደረጉት ብቻ ሳይሆን '' ውሸት ሲደጋገም እውነት የመሆን እድልይኖረዋል'' የሚለውን ብሂል ሁል ጊዜ የሚሰራ ስለመሰላቸው ብቻ ነው።ሕዝቡማ ችግር የለበትም:: የተባበሩት መግስታት ሰራዊት ኖረም አልኖረም ከመረብ ማዶው ወደመረብ ወዲሁ የመረብ ወዲሁም ወደ መረብ ማዶው ሄዶ '' ሮብ ገበያ''  ቅዳሜ ገበያ ብሎ ይገበያያል።ታሪክ ፀሐፊዎች ገና ብዙ ያልተፃፈ አዝመራ መኖሩን ባይዘነጉብንደስ ይላል። ፅሁፌን ከመጠቅለሌ በፊት   አንዲት ሃሳቤን የምታሳርግልኝ  ታዋቂው አሜሪካዊውን  ሀገራችን ታሪክ አዋቂ  አያሌ መፃህፍትን ስለ ኢትዮጵያ  ፃፉት አማርኛ አቀላጥፈው የሚናገሩት ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን  በተናገሩት ንግግር ልደምድም።
'' ኢትዮጵያን የሚያስተዳድሯት የሀገሪቱን  ታሪክ በሚገባ የማያውቁ ናቸው።ስለዚህ የምመክረው ታሪክን በደንብ ይረዱ ----እናንት ኢትዮጵያውያን የችግሮቻችሁሁሉ መፍቻ ታሪካችሁ ላይ አለ በደንብ ተረዱት'ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን ባለፈው አመት ለኢሳት ቴሌቭዥን ከተናገሩት።


አበቃሁ።
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ


የ ፅሁፉ መርጃዎች 

፩/ http://www.ethioobserver.net/forgoten_heroes.ሕትም በ ፍቅረ ቶሎሳ 

፪/ኢሳት ራድዮ የካቲት 11/2004 ዓም 

፫/ግሎባል አልያንስ ኢትዮጵያ http://www.globalallianceforethiopia.org 

ምንጭ gudayachn

No comments:

Post a Comment